“ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

የቀድሞ ክለቡን ሊቨርፑል በማክሰኞ ምሽት የቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ የሚገጥመው ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ በልጅነቱ ወቅት ስቴቨን ጄራርድ እና ዣቢ አሎንሶን ያደንቅ እንደነበር ተናግሯል፡፡ አርኖልድ ይህንን የተናገረው ከአማዞን ፕራይም ጋር በነበረው ቆይታ ሲሆን ኳስን ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ መማሩን ጠቅሷል፡፡ “ በጣም አሪፍ የሆነን ኳስ ሲመታ በሚያወጣው ድምጽ መለየት ይቻላል ፤ ለመግለጽ ቢያስቸግርም ጥሩ የሆነ እና በትክክል የተመታ ኳስ በድምጹ ያስታውቃል፤ አሎንሶ የተለያዩ አይነት የማቀበል ቴክኒኮችን እንድሞክር ምክንያቴ ሆኗል፤ አሁን አሰልጣኝ ሆኖ እንኳን ያን ብቃት አብሮት አለ” በማለት ትሬንት ተናግሯል፡፡

ትሬንት በነጻ ዝውውር ሊቨርፑል በመልቀቅ ሪያል ማድሪድን ከተቀላቀለ በኋላ ድንቅ አቋሙን ለማግኘት ጊዜ የፈጀበት ሲሆን በጉዳት ምክንያትም ተደጋጋሚ የቋሚነት እድልን ማግኘት አልቻለም፡፡ ከሊቨርፑል ጋር በሚደረገው ጨዋታ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ይገባል ወይ የሚለው ጉዳይ ይጠበቃል፡፡  

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    Diribe Welteji banned for two years

    The Court of Arbitration for Sport (CAS) has partially upheld an appeal by World Athletics against the Ethiopian National Anti-Doping Office (ETH-NADO) and middle-distance runner Diribe Welteji Kejelcha (Ethiopia). Ms…

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    የቀድሞው የቼልሲ የመሀል ተከላካይ ጆን ቴሪ ጥር ላይ በተሰናበቱት አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ ምትክ የጊዜያዊ አሰልጣኝነት እድል ባለማግኘቱ ደስተኛ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡  ጆን ቴሪ በቼልሲ አካዳሚ በበጎ ፈቃድ አሰልጣኝነት በወር ሁለት ቀን…

    You Missed

    Ethiopia Bunna appoints new chairman 

    Ethiopia Bunna appoints new chairman 

    Diribe Welteji banned for two years

    Diribe Welteji banned for two years

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

    ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

    ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ