አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ የ2.8 ሚሊዮን ብር እና 40 ግራም የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበረከተላት።

(ስፖርት ኮሚሽን)

በቶኪዮ 2020 ፖራሊምፒክ ጨዋታ በ1500 ሜትር T-13 አይነስውራን ጭላንጭል ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስመዘገበችው አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ የ2.8 ሚሊዮን ብር እና 40 ግራም የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል ።

አትሌት ትዕግሥት ገዛኸኝ 04:23:24 በሆነ ሰዓት በመግባት ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ በማስመዝገብ በፖራሊምፒክ ጨዋታ ታሪክ መስራቷ ይታወሳል ።

የቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ንጋቱ ኃ/ማሪያም 400 ሺህ ብር ሲሸለም ፤

በ1500 ሜትር እጅ ጉዳት T-46 5ኛ ደረጃን በመያዝ ዲፕሎማ ያስመዘገበው አትሌት ገመቹ አመኑ የ200ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

በተመሳሳይ በ1500 ሜትር አይነስውራን ጭላንጭል T-13 7ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው አትሌት ታምሩ ከፍያለው 150 ሺህ ብር ተሸልሟል ።

የቡድኑ ሀኪም 100 ሺህ ብር ተሸልሟል ።

በቶኪዮ 2020 ፖራሊምፒክ ጨዋታ ኢትዮጵያ በ 3 አትሌቶች የተወከለች ሲሆን 1 ወርቅ ሁለት ዲፕሎማ በማግኘት ከዓለም 59ኛ ከአፍሪካ 6ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች ።

  • Related Posts

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

    በበረከት ጸጋዬ 35ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ (ከታህሳስ 21 እስከ ጥር 10/2018) በሞሮኮ የሚካሄድ ሲሆን የወቅቱ ሻምፒዮን አይቮሪኮስት :ደቡብ አፍሪካ እና መሰል ሀገራት ከሚቀጥለው አመት የፊፋ የአለም ዋንጫ ቀደም ብለው በአህጉራዊ ውድድሩ…

    ሞ ሳላህ ላይ እየተሰጡ ያሉ ትችቶች እንዴት ይታያሉ? 

    ግብጻዊው የሊቨርፑል የፊት መስመር ተጫዋች ሞ ሳላህ ከሊዲሱ ጨዋታ መልስ በሰጠው አስተያየት መነጋገሪያ ሆኖ ከርሟል፡፡  “ 90 ደቂቃ ሙሉ ተጠባባቂ ወንበር ላይ መሆኔን ላምን አልችልም፡፡ ለሶስተኛ ተከታታይ ጨዋታ ነው ይህ…

    Leave a Reply

    You Missed

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

    ሞ ሳላህ ላይ እየተሰጡ ያሉ ትችቶች እንዴት ይታያሉ? 

    ሞ ሳላህ ላይ እየተሰጡ ያሉ ትችቶች እንዴት ይታያሉ? 

    ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች

    ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች

    Qatar to build 11 running tracks in 11 countries

    Qatar to build 11 running tracks in 11 countries

    በአፍሪካ ትምህርት ቤቶች የእግር ኳስ ሻምፕዮና የሴካፋ ማጣሪያ ኢትዮጵያ በሁለቱም ጾታ ለፍጻሜ አለፈች

    በአፍሪካ ትምህርት ቤቶች የእግር ኳስ ሻምፕዮና የሴካፋ ማጣሪያ ኢትዮጵያ በሁለቱም ጾታ ለፍጻሜ አለፈች

    ቀይ ቀበሮዎቹ ካታር ለመገኘት በሞሮኮ ይፋለማሉ

    ቀይ ቀበሮዎቹ ካታር ለመገኘት በሞሮኮ ይፋለማሉ