“ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

የቀድሞ ክለቡን ሊቨርፑል በማክሰኞ ምሽት የቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ የሚገጥመው ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ በልጅነቱ ወቅት ስቴቨን ጄራርድ እና ዣቢ አሎንሶን ያደንቅ እንደነበር ተናግሯል፡፡ አርኖልድ ይህንን የተናገረው ከአማዞን ፕራይም ጋር በነበረው ቆይታ ሲሆን ኳስን ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ መማሩን ጠቅሷል፡፡ “ በጣም አሪፍ የሆነን ኳስ ሲመታ በሚያወጣው ድምጽ መለየት ይቻላል ፤ ለመግለጽ ቢያስቸግርም ጥሩ የሆነ እና በትክክል የተመታ ኳስ በድምጹ ያስታውቃል፤ አሎንሶ የተለያዩ አይነት የማቀበል ቴክኒኮችን እንድሞክር ምክንያቴ ሆኗል፤ አሁን አሰልጣኝ ሆኖ እንኳን ያን ብቃት አብሮት አለ” በማለት ትሬንት ተናግሯል፡፡

ትሬንት በነጻ ዝውውር ሊቨርፑል በመልቀቅ ሪያል ማድሪድን ከተቀላቀለ በኋላ ድንቅ አቋሙን ለማግኘት ጊዜ የፈጀበት ሲሆን በጉዳት ምክንያትም ተደጋጋሚ የቋሚነት እድልን ማግኘት አልቻለም፡፡ ከሊቨርፑል ጋር በሚደረገው ጨዋታ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ይገባል ወይ የሚለው ጉዳይ ይጠበቃል፡፡  

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Decorated two-time former World champion and Olympic medallist, Gudaf Tsegay, has been banned for four months by the Athletics Integrity Unit (AIU) under a Case Resolution Agreement, after admitting to…

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    The Ethiopia national under-17 football team will face Mozambique national under-17 football team in a play-off match that will determine qualification for the FIFA U-17 World Cup. Ethiopia defeated Tunisia…

    You Missed

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

    Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

    CBE Crowned Women’s Premier League Champions

    CBE Crowned Women’s Premier League Champions

    Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

    Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች