ፌዴሬሽኑ እና የሊግ ተሳታፊዎችን ቁጥር ማሳደግ

  • amharic
  • August 12, 2025
  • 0 Comments

ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ሲዳማ ቡና የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት /ካስ/ የፅሁፍ ምልልስ የተረዳሁት ነገር ፌዴሬሽኑ የፕሪምየር ሊግ ክለቦችን 20 ለማድረግ ያቀረበው ምክንያት ምንም አይነት ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን ነው::

እንደምታስታውሱት ፌዴሬሽኑ ሊጉን ወደ 20 ክለቦች ለማሳደግ ያቀረበው ምክንያት በፕሪምየር ሊጉ የፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከተመረመሩት እና በኋላም ከተቀጡት አራት ክለቦች ውጭ ያሉት ክለቦች አለመመርመራቸውን እና በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ መሰረት ከጥፋት ነፃ መሆናቸው አለመረጋገጡ ነው::

ምስል 1- የፌደሬሽን ምክንያት

ሲዳማ ቡና ለ”ካስ” ባስገባው መከራከሪያ ሌሎቹ ክለቦች አለመመርመራቸውን በምክንያት በማቅረብ ምርመራው በዘፈቀደ የተደረገ መሆኑን ይገልፃል:: በዚህም አራቱ ክለቦች ተለይተው መቀጣታቸው አድሏዊ እና ኢፍትሀዊ [የውድድር] ከባቢ በመፍጠር ሲዳማ ቡና እና ሌሎቹ ሶስት ክለቦች ተገቢ ያልሆነ ኢላማ እንዲሆኑ ተደርገዋል ይላል:: (ምርመራውን ያደረገው ፌዴሬሽኑ እንዳልሆነ ልብ ይሏል)


ፌዴሬሽኑ በምላሹ በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ መሰረት የፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴው ክለቦችን በዘፈቀደ መርጦ የመመርመር መብት እንዳለው ገልፇል:: ስለዚህ ሲዳማ ቡና እና ሌሎች ሶስት ክለቦች ተለይተው መመርመራቸው እና መቀጣታቸው የህግ ጥሰት እንደሌለበት በፅሁፍ ተከራክሯል::


የእኔ ጥያቄ እዚህ ላይ ነው:: በፌዴሬሽኑ የህግ ምላሽ መሰረት የ14ቱ ክለቦች አለመመርመር ምንም አይነት የህግ ጥሰት ከሌለበት “ገና ለገና አጥፍተው ይሆናል: ነፃ አይሆኑም” በሚል የሊጉን ተሳታፊዎች ቁጥር ማሳደግ የህግ መሰረቱ ምንድን ነው? ክለቦቹ በእግር ኳሱ የፍትህ አካላት ጥፋተኛ እስኪባሉ ድረስ ነፃ መሆናቸውንስ አይቃረንም? ፌዴሬሽኑ ለ”ካስ” የህግ ጥሰት የለም እያለ በሀገር ውስጥ ውሳኔዎቹ ግን ስህተት እንዳለ የሚያሳይ ውሳኔ መወሰኑ አይቃረንም?

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

የጀርመን ብሄራዊ ቡድን የ2014ቱን የአለም ዋንጫ ካሸነፉ ማግስት አንድ ከባድ ነገርን መጋፈጥ ነበረባቸው:: ኑሮ ያለድንቁ አጥቂ ሚሮስላቭ ክሎዘ! በአሁኑ ሰአት በጀርመን ሁለተኛ ዲቪዚዮን የቡንደስሊጋ ዋንጫን ብዙ ጊዜ በማሸነፍ ሁለተኛ ላይ…

የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

ከኬንያ አንጋፋ የረጅም ርቀት ሩጫ አትሌቶች መካከል ሦስቱ – ፖል ቴርጋት፣ ዳንኤል ኮመን እና ሞሰስ ታኑይ – እሁድ ህዳር 14 ቀን 2018 በሚካሄደው የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዓለም…

You Missed

ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

Chelsea Fans Can’t Connect With Squad, But Maresca Needs Time

Chelsea Fans Can’t Connect With Squad, But Maresca Needs Time

የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

“ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

“ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

Wanda Diamond League season calendar confirmed for 2026

Wanda Diamond League season calendar confirmed for 2026