በታላላቆቹ የአውሮፓ ሊጎች ግቦችን እያመረቱ ያሉ አምስት ተጫዋቾች

በዘንድሮው የውድድር ዘመን በአምስቱ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ከዚህ በፊት በግብ አስቆጣሪነታቸው የሚታወቁት ተጫዋቾች አሁንም ግብ ማምረታቸውን ቀጥለውበታል፡፡ እንደሀሪ ኬን ፤ አርሊንግ ሀላንድ እና ኪሊያን ምባፔ ያሉ ተጫዋቾች በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ግንባር ቀደም ናቸው፡፡

እንደስፖርቲንግ ፔዲያ ዘገባ ከሆነ ደግሞ የሞናኮው የፊት መስመር ተጫዋች አንሱ ፋቲ በወጥነት እንደዚሁም እድሎችን በመጠቀም አንጻር በአውሮፓ ያሉትን ታላላቅ አጥቂዎች እንደሚበልጣቸው ቁጥራዊ መረጃዎችን አስደግፎ አቅርቧል፡፡

አንሱ ፋቲ በተሰለፈባቸው ሁሉም የሞናኮ ጨዋታዎች ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡ በ3 የሊግ ጨዋታዎች 5 ግቦች አሉት፡፡  ይህም በየ32 ደቂቃው ግቦችን እንደሚያስቆጥር ማሳያ ነው፡፡ ፋቲ ምንም እንኳን ለረጅም ጊዜ በጉዳት ርቆ የቆየ ቢሆንም ወዲያውኑ ወደግብ ማግባቱ መመለስ ችሏል፡፡ እንደአንሱ ፋቲ በተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሁሉ ግብ ማስቆጠር የቻለው ሀሪ ኬን ሲሆን በየ45 ደቂቃው ግብ እንደሚያስቆጥር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሀላንድ ግቦችን በየ66 ደቂቃ የሚያስቆጥር ሲሆን ምባፔ በበኩሉ በየ72 ደቂቃው ግቦችን ያስቆጥራል፡፡

የአይንትራክት ፍራንክፈርቱ ወጣት ተጫዋች ካን ኡዙን በተሰለፈባቸው 80% ጨዋታዎች ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡

ሀላንድን የሚጠጋ ሪከርድ በፕሪሚየር ሊጉ ያለው የቦርንማውዙ አጥቂ አንትዎን ሴሜንዮ ሲሆን በተሰለፈባቸው 57% ጨዋታዎች ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

Brook Genene

Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine. He also has over a decade of experience covering the Bundesliga and German football for several outlets.

Related Posts

ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ያለፉት ሀገራት እነማን ናቸው?

በፊፋ የዓለም ዋንጫ የማጣሪያ ውድድሮች እየተካሄዱ ሲሆን ከአውሮፓ እግር ኳስ ማሀበር እና ሰሜን እና መካከለኛው አሜሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን አባላት በስተቀር ሌሎቹ ኮንፌዴሬሽኖች በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ውድድር…

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

© Getty Images ኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ፈይሳ በባንክ ኦፍ አሜሪካ ቺካጎ ማራቶን ባለድል ሆናለች። መገርቱ አለሙ ደግሞ በሁለተኛነት አጠናቅቃለች። ሐዊ ውድድሩን ያሸነፈችበት ጊዜ 2:14:56 ሲሆን የግሏ ምርጥ ሰዓት ነው።  የዓለም ማራቶን ሜጀር…

You Missed

በታላላቆቹ የአውሮፓ ሊጎች ግቦችን እያመረቱ ያሉ አምስት ተጫዋቾች

በታላላቆቹ የአውሮፓ ሊጎች ግቦችን እያመረቱ ያሉ አምስት ተጫዋቾች

ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ያለፉት ሀገራት እነማን ናቸው?

ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ያለፉት ሀገራት እነማን ናቸው?

St. George wins the City Cup 

St. George wins the City Cup 

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው