የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ቀጣይ እጣ ፈንታ ምንድን ነው?

  • Feature
  • September 10, 2023
  • 0 Comments

ዋልያዎቹ በ4 ነጥብ ከምድባቸው መጨረሻ በማጠናቀቅ አይቮሪ ኮስት ለምታዘጋጀው አፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ በሀገር ውስጥ ጨዋታን ለማድረግ ያልታደለው ብሄራዊ ቡድን በሜዳም ከሜዳ ውጭም በርካታ ፈተናዎች እየገጠሙት ይገኛሉ፡፡

Picture- Ethiopian Football Federation

የአዲስ አበባ ስቴዲየም እድሳት በተያዘለት ቀነ ገደብ አለማለቅ፤ የተተከለው ሳር ድጋሚ ተነስቶ በሌላ እንዲተካ መወሰን፤ የአደይ አበባ ስቴዲየም ግንባታ በተለያዩ አስተዳደራዊ ችግሮች ምክንያት መጓተት እና የሜዳ ጨዋታዎችን ከሀገር ውጭ ለማከናወን እየወጣ ያለው ከፍተኛ ገንዘብ ብሄራዊ ቡድኑ ከሜዳ ውጭ ከተጋረጡበት ችግሮች መካከል የሚጠቀሱት ናቸው፡፡

ፌደሬሽኑ ምንም እንኳን ከአጋር ድርጅቶች ጋር ስምምነቶችን በመፈጸም ራሱን በፋይናንሱ ረገድ ለማጠናከር የተለያዩ ጥረቶችን ቢያደርግም እስከመቼ ድረስ ጨዋታዎችን ከሜዳ ውጭ እያሰናዳ ይዘልቃል የሚለው ነገር ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው፡፡

ሜዳ ላይም ቢሆን ብሄራዊ ቡድኑ ውጤት ከራቀው ሰንበትበት ብሏል፡፡ ሰኔ 2014 ላይ ግብጽ ላይ የተመዘገበው ድል ብዙዎችን ያስፈነደቀ ቢሆንም እናም ከጥቂት ወራት በኋላም ለአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የዋልያዎቹ ቆይታ እንደአንድ ምክንያት ቢጠቀስም ከዛ በኋላ የተደረጉት የማጣሪያ ጨዋታዎች ደካማ የነበሩ እና ከውጤት ማጣቱም ጋር ተያይዞ ለአሰልጣኙ በፈቃድ ስራ የመልቀቅ እንደ አንድ ምክንያት ሆነዋል፡፡

በአሰልጣኝ ውበቱ ስር ኳስን ከኋላ መስርቶ እና ተቆጣጥሮ ለመጫወት የሚጥርን ቡድን የመስራቱ ሂደት ለቻን እና ለአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ማሳለፍ ቢችልም በውድድር ግጥሚያዎች ላይ የታየው እንቅስቃሴ ግን እጅጉን ደካማ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ብዙ ኳሶችን አደጋኛ ባልሆነ የሜዳ ክፍል የሚቀባበል እና በርካታ የሚባሉ ጥራት ያላቸው እድሎችን ለመፍጠር የሚቸገር ቡድንን አስተውለናል፡፡ ይህ ደግሞ ውጤታማነቱን እጅጉን ጎድቶታል፡፡ ቀላል በሚባሉ የተከላካይ መስመር ስህተቶችም ግብ እየተቆጠረበት ለሚያስቆጩ ሽንፈቶች ተጋላጭ ሲሆን አይተናል፡፡

ከውበቱ መልቀቅ በኋላም ቡድኑ ከማላዊ ጋር 0-0 ሲለያይ ባለፈው አርብ ደግሞ በግብፅ 1-0 ተረቷል፡፡ አሁን ትልቁ ጥያቄ የሚሆነው በሚዲያዉም ሆነ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያለው እና ቡድኑን አንድ ደረጃ ወደፊት ፈቀቅ ሊያደርግ የሚችል አሰልጣኝ ማነው የሚለው ነው፡፡

ውበቱ በተደጋጋሚ ከሚዲያ ይደርስበት የነበረው ጫና ከመጠን ያለፈ እንደነበር በመግለጫዎቹም ሆነ በተጋበዘባቸው ፕሮግራሞች ላይ ሲናገር ተስተውሏል፡፡ ይህ ሞቃቱ የብሄራዊ ቡድን ወንበር የሚመች ሊሆን እንደማይችል ይጠበቃል፡፡ አሁን በሊጉ ውስጥ ካሉ አሰልጣኞችም የትኛው ለብሄራዊ ቡድን ይሆናል የሚለው ጉዳይ ብዙዎችን እንደሚያከራክር ይጠበቃል፡፡ ምናልባትም አይንን ወደ ውጭ ሀገር አሰልጣኝ ማዞር የሚያስፈልግበት ደረጃ ላይ ሳንደርስ አልቀረንም፡፡ እዚህ ላይም ቢሆን ግን የቅርብ አመታት ተሞክሮን ግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ምርጫ የማይስማማቸው ብዙዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ይታሰባል፡፡

ከህዳር ወር ጀምሮ ለ2026ቱ አለም ዋንጫ የማጣሪ ጨዋታዎችን ማድረግ የሚጀምረው ቡድን በቀጣዮች ጥቂት ወራት ሁሉንም እንኳን ባይባል አንገብጋቢዎቹን ጉዳዮች መፍትሄ በማበጀት የተሻለ እንቅስቃሴን ማሳየት ይኖርበታል፡፡

Picture- Ethiopian Football Federation

ብሄራዊ ቡድኑ ፈረንጆቹ እንደሚሉት መስቀለኛ መንገድ ላይ ይገኛል፡፡ በቀጣይ ከአሰልጣኝ፤ ከሜዳ እናም በአጠቃላይ ከአስተዳደር አንጻር የሚወሰኑ ውሳኔዎች ትልቅ አንድምታ እንደሚኖራቸው እሙን ነው፡፡ በብዙ ችግር ላይ ያለው ብሄራዊ ቡድን ህመሙን የሚያስታግስለት መድሃኒት በአስቸኳይ ይፈልጋል፡፡

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine. He also has over a decade of experience covering the Bundesliga and German football for several outlets.

    Related Posts

    በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዙሪያ የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት ምን ይላል?

    ከአራት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብን “የታገዱ ተጫዋቾችን በማሰለፍ” በሚል በኢትዮጵያ ዋንጫ ያገኘው ድል ተሰርዞ በፎርፌ እንዲሽነፍ እና የቀጣዩ የውድድር ዘመን የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ…

    ሊቨርፑል ወደ’ንግስናው’ ተመልሷል

    “My greatest challenge is not what’s happening at the moment, my greatest challenge was knocking Liverpool right off their f*g perch. And you can print that” ይህን ያሉት ሰር አሌክስ…

    Leave a Reply

    You Missed

    St. George wins the City Cup 

    St. George wins the City Cup 

    ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

    ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

    Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

    Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

    Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

    Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

    የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ

    የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ