“ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

የቀድሞ ክለቡን ሊቨርፑል በማክሰኞ ምሽት የቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ የሚገጥመው ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ በልጅነቱ ወቅት ስቴቨን ጄራርድ እና ዣቢ አሎንሶን ያደንቅ እንደነበር ተናግሯል፡፡ አርኖልድ ይህንን የተናገረው ከአማዞን ፕራይም ጋር በነበረው ቆይታ ሲሆን ኳስን ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ መማሩን ጠቅሷል፡፡ “ በጣም አሪፍ የሆነን ኳስ ሲመታ በሚያወጣው ድምጽ መለየት ይቻላል ፤ ለመግለጽ ቢያስቸግርም ጥሩ የሆነ እና በትክክል የተመታ ኳስ በድምጹ ያስታውቃል፤ አሎንሶ የተለያዩ አይነት የማቀበል ቴክኒኮችን እንድሞክር ምክንያቴ ሆኗል፤ አሁን አሰልጣኝ ሆኖ እንኳን ያን ብቃት አብሮት አለ” በማለት ትሬንት ተናግሯል፡፡

ትሬንት በነጻ ዝውውር ሊቨርፑል በመልቀቅ ሪያል ማድሪድን ከተቀላቀለ በኋላ ድንቅ አቋሙን ለማግኘት ጊዜ የፈጀበት ሲሆን በጉዳት ምክንያትም ተደጋጋሚ የቋሚነት እድልን ማግኘት አልቻለም፡፡ ከሊቨርፑል ጋር በሚደረገው ጨዋታ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ይገባል ወይ የሚለው ጉዳይ ይጠበቃል፡፡  

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

    የጀርመን ብሄራዊ ቡድን የ2014ቱን የአለም ዋንጫ ካሸነፉ ማግስት አንድ ከባድ ነገርን መጋፈጥ ነበረባቸው:: ኑሮ ያለድንቁ አጥቂ ሚሮስላቭ ክሎዘ! በአሁኑ ሰአት በጀርመን ሁለተኛ ዲቪዚዮን የቡንደስሊጋ ዋንጫን ብዙ ጊዜ በማሸነፍ ሁለተኛ ላይ…

    CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

    This year’s edition of the CECAFA U-17 tournament will officially kick off on Saturday in Ethiopia. Ten countries will take part in the competition the list of which includes hosts…

    You Missed

    ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

    ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

    CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

    CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

    Chelsea Fans Can’t Connect With Squad, But Maresca Needs Time

    Chelsea Fans Can’t Connect With Squad, But Maresca Needs Time

    የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

    የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

    “ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

    “ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

    Wanda Diamond League season calendar confirmed for 2026

    Wanda Diamond League season calendar confirmed for 2026