አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ የ2.8 ሚሊዮን ብር እና 40 ግራም የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበረከተላት።

(ስፖርት ኮሚሽን)

በቶኪዮ 2020 ፖራሊምፒክ ጨዋታ በ1500 ሜትር T-13 አይነስውራን ጭላንጭል ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስመዘገበችው አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ የ2.8 ሚሊዮን ብር እና 40 ግራም የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል ።

አትሌት ትዕግሥት ገዛኸኝ 04:23:24 በሆነ ሰዓት በመግባት ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ በማስመዝገብ በፖራሊምፒክ ጨዋታ ታሪክ መስራቷ ይታወሳል ።

የቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ንጋቱ ኃ/ማሪያም 400 ሺህ ብር ሲሸለም ፤

በ1500 ሜትር እጅ ጉዳት T-46 5ኛ ደረጃን በመያዝ ዲፕሎማ ያስመዘገበው አትሌት ገመቹ አመኑ የ200ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

በተመሳሳይ በ1500 ሜትር አይነስውራን ጭላንጭል T-13 7ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው አትሌት ታምሩ ከፍያለው 150 ሺህ ብር ተሸልሟል ።

የቡድኑ ሀኪም 100 ሺህ ብር ተሸልሟል ።

በቶኪዮ 2020 ፖራሊምፒክ ጨዋታ ኢትዮጵያ በ 3 አትሌቶች የተወከለች ሲሆን 1 ወርቅ ሁለት ዲፕሎማ በማግኘት ከዓለም 59ኛ ከአፍሪካ 6ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች ።

  • Related Posts

    St. George wins the City Cup 

    Ethiopia’s oldest and most successful club St. George have added another trophy to their cabinet by winning the 19th edition of the Addis Ababa City Cup. This is the club’s…

    ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

    © Getty Images ኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ፈይሳ በባንክ ኦፍ አሜሪካ ቺካጎ ማራቶን ባለድል ሆናለች። መገርቱ አለሙ ደግሞ በሁለተኛነት አጠናቅቃለች። ሐዊ ውድድሩን ያሸነፈችበት ጊዜ 2:14:56 ሲሆን የግሏ ምርጥ ሰዓት ነው።  የዓለም ማራቶን ሜጀር…

    Leave a Reply

    You Missed

    St. George wins the City Cup 

    St. George wins the City Cup 

    ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

    ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

    Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

    Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

    Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

    Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

    የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ

    የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ