ሞ ሳላህ ላይ እየተሰጡ ያሉ ትችቶች እንዴት ይታያሉ? 

ግብጻዊው የሊቨርፑል የፊት መስመር ተጫዋች ሞ ሳላህ ከሊዲሱ ጨዋታ መልስ በሰጠው አስተያየት መነጋገሪያ ሆኖ ከርሟል፡፡ 

“ 90 ደቂቃ ሙሉ ተጠባባቂ ወንበር ላይ መሆኔን ላምን አልችልም፡፡ ለሶስተኛ ተከታታይ ጨዋታ ነው ይህ የሆነው፡፡ በእግር ኳስ ዘመኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ይመስለኛል፡፡ ላለፉት አመታት ለዚህ ክለብ በርካታ ነገሮችን አድርጌያለሁ በተለይም ደግሞ ያለፈው አመት” በማለት ነበር ሳላህ ከሊድስ ጨዋታ በኋላ ለጋዜጠኞች አስተያየቱን የሰጠው፡፡ 

ሳላህ ለ7 ደቂቃ ያህል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለሊቨርፑል ውጤት አለመሳካት እርሱን ተጠያቂ ለማድረግ የፈለገ ሰው እንዳለ ተናግሯል፡፡ ከአሰልጣኙ አርነ ስሎት ጋር ያላቸውን ግንኙነት የተቸ ሲሆን ከዛም በተጨማሪ እንደጄሚ ካራገር ካሉ ተንታኞች ሊሰነዘርበት የሚችለውን ትችት አስቀድሞ ተናግሯል፡፡ 

ሳላህ አያይዞም ከዚህ በፊት ሀሪ ኬን ጋር በተገናኘ ተፈጥሮ ስለነበረው ሁኔታ ተናግሯል፡፡ እርሱ በዛ ቦታ ቢሆንም ሊደርስበት ይችል የነበረውን ትችት እና ተቃውሞ አያይዞ ገልጿል፡፡ 

ከሳላህ አስተያየት በኋላ በርካታ የሚዲያ ሰዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል አየርላንዳዊው የቀድሞው የሊቨርፑል ተጫዋች ጄሰን ማከቲር ይገኝበታል፡፡ ማከቲር ሳላህ ሊቨርፑል ተሸክሞ እንደማያውቅ እና ክለቡን የተሸከመ ተጫዋች ይጠቀስ ቢባል ስቴቨን ጄራርድ ምሳሌ መሆኑን ጠቅሷል፡፡ ሳላህ የሚወደስ ከሆነም እንደጆርዳን ሄንደርሰን አይነት ተጫዋቾች መነሳት እና መደነቅ አለበት በማለት ተናግሯል፡፡ 

ጄሚ ካራገርም እንደተጠበቀው በስካይ ስፖርት ‘Monday Night Football’ ፕሮግራሙ ላይ ሳላህ ከሊቨርፑል በፊት ይህ ነው የማይባል ተጫዋች እንደሆነ ተናግሯል፡፡ ከሊቨርፑል በፊት ሳላህ የሚታወቀው በቻልሲ ያልተሳካለት ተጫዋች በመባል ነው ያለው ካራገር ከዚህም በተጨማሪ ከሀገሩ ግብጽ ጋር እንኳን ዋንጫን አላሸነፈም ብሏል፡፡ 

ከበርካታ ስፍራዎች ሳላህ ትችቶች ገጥመውታል፡፡ ምናልባትም አነጋጋሪው መግለጫ ሲሰጥ ይህ ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል፡፡ ነገር ግን የተሰጡት አስተያየቶች በጣም የተጋነኑ እና መስመርን የሳቱ ይመስላሉ፡፡ 

አብዛኞቹ አስተያየቶች ሳላህ ከዚህ በፊት በቂ ግልጋሎትን እንዳልሰጠ የሚያስመስሉ እና ያሳያቸውን ድንቅ እንቅስቃሴዎች የዘነጉ ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ ከማከቲር እና ካራገር አስተያየቶችም መረዳት የምንችለው ይህንን ነው፡፡ 

ሳላህን ሙሉ በሙሉ ጫና ውስጥ መክተት እና ስሙን ማጠልሸት የሚመስሉ አስተያየቶችን አስተውለናል፡፡ ሳላህ ሊቨርፑል ከ30 አመታት በኋላ ላሳኩት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ እንደዚሁም ከ14 አመታት በኋላ ላስመዘገቡት የቻፒዮንስ ሊግ ድል ወሳኙን ሚና ተጫውቷል፡፡ 

ሳላህ ባለፉት አመታት ሊቨርፑል ካሳካቸው ድል ጋር ስሙ ጎን ለጎን የሚነሳ ተጫዋች ነው፡፡ እርግጥ ነው የአሰልጣኝን ውሳኔ ማክበር እና ለቡድን አጋሮቹ አክብሮትን ማሳየት ግዴታው ነው፡፡ በእርሱ ላይ የተነሱ አብዛኞቹ አስተያየቶች ግን ምክንያታዊነትን የተከተሉ አይመስሉም፡፡

ለምሳሌ ያህል በዘንድሮው የውድድር ዘመን ያደረጋቸውን እንቅስቃሴዎች ብንመለከት ሳላህ ከየተኛው የሊቨርፑል ተጫዋች የበለጠ በርካታ እድሎችን እንደፈጠረ ኦፕታ ያሳያል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በፍጹም ቅጣት ምት ሳጥን ውስጥ በርካታ ኳሶችን አቀብሏል፡፡ በሌሎች የማጥቃት ንጻሬዎች ፊት ላይ እንዲቀመጥ የሚያደርጉ ቁጥሮች አሉት፡፡ በመከላከሉ ረገድም ከሌላኛው የክንፍ ተጫዋች ኮዲ ጋክፖ ይልቅ በርካታ የሜዳ ክልልን ሸፍኗል፡፡ ስለዚህ ተጠባባቂ ወንበር ላይ እርሱን ለማስቀመጥ ሆነ የሊቨርፑል ውጤት ማጣት የእርሱ ጥፋት ነው ለማለት በቂ መረጃ የለም፡፡ እየተሰነዘሩ ያሉት ትችቶች አግባብ አይደሉም የሚባለው ከዚህ በመነጨ ነው፡፡

Brook Genene

Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

Related Posts

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

The Ethiopia national under-17 football team will face Mozambique national under-17 football team in a play-off match that will determine qualification for the FIFA U-17 World Cup. Ethiopia defeated Tunisia…

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

You Missed

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix