በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዙሪያ የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት ምን ይላል?

ከአራት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብን “የታገዱ ተጫዋቾችን በማሰለፍ” በሚል በኢትዮጵያ ዋንጫ ያገኘው ድል ተሰርዞ በፎርፌ እንዲሽነፍ እና የቀጣዩ የውድድር ዘመን የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳታፊነቱ እንዲነጠቅ መወሰኑ ይታወሳል። በዚህም ክለቡ ለዓለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት /ካስ/ ይግባኝ እንደጠየቀ መግለፁ ይታወቃል።

ይግባኙ ምን ላይ ደርሷል?

ካስ በገላጋዮች የሚሰሙ ክርክሮችን ዝርዝር በየሳምንቱ ወይም እንደ አስፈላጊነቱ በድረ ገፁ ያወጣል። የሲዳማ ቡና ጉዳይ ግን እስካሁን ድረስ በዚህ ዝርዝር ውስጥ አልተካተተም።  ካስ ይግባኙ ደርሶት እንደሆነ እና ክርክሩ መቼ ሊሰማ እንደሚችል ጠይቄያለሁ። 

ካስ በምላሹ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ላይ ያቀረበውን ይግባኝ ሐምሌ ስምንት ቀን 2017 ዓ.ም መቀበሉን አረጋግጧል። 

በአሁኑ ወቅት ሁለቱ ተከራካሪዎች ጉዳያቸውን በፅሁፍ እያቀረቡ እንደሆነም ካስ ገልፅዋል። ይህ ወቅት ሁለቱ ወገኖች ክርክራቸውን፣ ማስረጃዎቻቸውን እና የህግ ምክንያቶቻቸውን በፅሁፍ ለካስ የሚያቃርቡበት ጊዜ ነው።

ሆኖም ካስ ክርክሩን የመስሚያ ቀን አልቆረጠለትም። ካስ ክርክሩን የመስሚያ ቀን እንደወሰነ በድረ ገፁ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

The Ethiopia national under-17 football team will face Mozambique national under-17 football team in a play-off match that will determine qualification for the FIFA U-17 World Cup. Ethiopia defeated Tunisia…

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

You Missed

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix