በታላላቆቹ የአውሮፓ ሊጎች ግቦችን እያመረቱ ያሉ አምስት ተጫዋቾች

በዘንድሮው የውድድር ዘመን በአምስቱ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ከዚህ በፊት በግብ አስቆጣሪነታቸው የሚታወቁት ተጫዋቾች አሁንም ግብ ማምረታቸውን ቀጥለውበታል፡፡ እንደሀሪ ኬን ፤ አርሊንግ ሀላንድ እና ኪሊያን ምባፔ ያሉ ተጫዋቾች በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ግንባር ቀደም ናቸው፡፡

እንደስፖርቲንግ ፔዲያ ዘገባ ከሆነ ደግሞ የሞናኮው የፊት መስመር ተጫዋች አንሱ ፋቲ በወጥነት እንደዚሁም እድሎችን በመጠቀም አንጻር በአውሮፓ ያሉትን ታላላቅ አጥቂዎች እንደሚበልጣቸው ቁጥራዊ መረጃዎችን አስደግፎ አቅርቧል፡፡

አንሱ ፋቲ በተሰለፈባቸው ሁሉም የሞናኮ ጨዋታዎች ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡ በ3 የሊግ ጨዋታዎች 5 ግቦች አሉት፡፡  ይህም በየ32 ደቂቃው ግቦችን እንደሚያስቆጥር ማሳያ ነው፡፡ ፋቲ ምንም እንኳን ለረጅም ጊዜ በጉዳት ርቆ የቆየ ቢሆንም ወዲያውኑ ወደግብ ማግባቱ መመለስ ችሏል፡፡ እንደአንሱ ፋቲ በተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሁሉ ግብ ማስቆጠር የቻለው ሀሪ ኬን ሲሆን በየ45 ደቂቃው ግብ እንደሚያስቆጥር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሀላንድ ግቦችን በየ66 ደቂቃ የሚያስቆጥር ሲሆን ምባፔ በበኩሉ በየ72 ደቂቃው ግቦችን ያስቆጥራል፡፡

የአይንትራክት ፍራንክፈርቱ ወጣት ተጫዋች ካን ኡዙን በተሰለፈባቸው 80% ጨዋታዎች ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡

ሀላንድን የሚጠጋ ሪከርድ በፕሪሚየር ሊጉ ያለው የቦርንማውዙ አጥቂ አንትዎን ሴሜንዮ ሲሆን በተሰለፈባቸው 57% ጨዋታዎች ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

Brook Genene

Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

Related Posts

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች የ4 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ‘ሌሎችን ለመርዳት እሮጣለሁ’ በተሰኘው የ2018 ሶፊማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለምአቀፍ 10ኪ.ሜ. የበጎ አድራጎት ዘመቻው አማካኝነት ያሰባሰበውን 4 ሚሊዮን ብር በቼሻየር ኢትዮጵያ መናገሻ ቢሮ በተከናወነ ደማቅ ስነ-ስርዓት ለተመረጡ…

You Missed

Gudaf Tsegay banned for four months

Gudaf Tsegay banned for four months

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች