ባንክ ኦፍ አሜሪካ የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. የስያሜ አጋር ሆነ

ከመጋቢት 2019 (March 2027) ጀምሮ ባንክ ኦፍ አሜሪካ ከአፍሪካ ትልቆቹ የሴቶች-ብቻ ሩጫ ውድድሮች አንዱ የሆነው ውድድር የስያሜ አጋር (Presenting Partner) ይሆናል።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከባንክ ኦፍ አሜሪካ ጋር እያሳደገ የሚገኘው አጋርነት አካል ሆኖ፣ ዓመታዊው ቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ውድድርም አዲስ የስያሜ ስፖንሰር (presenting sponsor) እንደሚኖረው ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ በህዳር ወር 2018ዓ.ም. የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መታወቂያ የሆነው የ10ኪ.ሜ. የጎዳና ሩጫ የስያሜ አጋር (Presenting Partner) እንደሚሆን ያሳወቀው ባንኩ፣ የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ.ን መጨመሩ የበለጡ ሰዎችን ወደረዥም ርቀት ሩጫ ለማምጣት የያዘውን ተልዕኮ እንዲያሰፋ እና በማህበረሰቡ ዘንድ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ እንዲያጠናክር ያስችለዋል፡፡

የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ሶስቱም ትልልቅ የሩጫ ሁነቶች (events) ፤ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ.፣ የልጆች ሩጫዎች እና የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ውድድሮች ላይ ባንክ ኦፍ አሜሪካ አዲሱ የስያሜ አጋር (Presenting Partner) ይሆናል።

ማህበረሰብን ያስቀደመ መርሆን መሰረት ያደረገው አጋርነት በርካታ ግቦችን ለማሳካት አቅዷል፡፡ ባንክ ኦፍ አሜሪካ በ10ኪ.ሜ. እና የልጆች ሩጫዎች ላይ ነፃ ተሳትፎዎችን በገንዘብ በመደገፍ የተሳታፊነትን ተደራሽነት የማስፋት ግብን ያግዛል፡፡ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ቀጣዩን የሯጮች ትውልድ የማበርታት ተልዕኮም ከባንኩ ልጆች እና ወጣቶች በስፖርት እንዲሳተፉ የበለጡ እድሎችን ከማቅረብ ዓለምአቀፍ ስትራቴጂ ጋር ይዛመዳል፡፡ ባንክ ኦፍ አሜሪካ በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለሚዘጋጁ ውድድሮች የሚውሉ ቴክኖሎጂዎችን ለማዘመን የሚያስችል ሀብትም ያቀርባል፤ ይህም በተራው የተሳታፊዎች ቁጥር ይበልጥ እንዲጨምር ያደርጋል፡፡

የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ፣ ባንክ ኦፍ አሜሪካ የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. አዲሱ የስያሜ አጋር መሆኑን ይፋ ሲያደርጉ ‹‹ባለፉት ሀያ ዓመታት የልጃገረዶች እና ሴቶች ዓመታዊ ሩጫችንን ለማሳደግ ብዙ ወጪ ፈሰስ አድርገናል፡፡ አሁን በባንክ ኦፍ አሜሪካ የአጋርነት ድጋፍ ደግሞ የበለጡ እድሎች ይከፈቱልናል፡፡ ባንክ ኦፍ አሜሪካ ለሩጫዎቻችን እና በሩጫዎቻችን አማካይነት ልናገለግላቸው ለምንሻው ማህበረሰቦች እንዲሁም ከሴቶች እና ልጆች ጋር ላሉን ሰፊ ስራዎች አብረውን ለመስራት ላሳዩት ቁርጠኝነት ላመሰግናቸው እፈልጋለሁ›› ብለዋል፡፡

በማርች 8 ከሚከበረው ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን ጋር ተያይዞ የሚዘጋጀው የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ባለፈው እሁድ 23ኛ ውድድሩን ሲያደርግ፣ ከ12ሺህ የበለጡ ተሳታፊዎችም ውድድሩን አጠናቅቀዋል፡፡ ከኢትዮጵያ የፖሊቲካ፣ ቢዝነስ እና ባህል ህይወት ብዙ ስመ-ጥር እንስቶችን እንዲሁም በኢትዮጵያ እያገለገሉ የሚገኙ በርካታ የውጪ አምባሳደሮችን የሚያሳትፈው ውድድር ተካፋዮቹ በኢትዮጵያ የሚኖሩ ሴቶችን ስኬቶች ለማክበር ሲሰባሰቡ የተለየ አይነት የህብረት ስሜት እንዲሰማቸው እንደሚያደርግ ተስተውሏል፡፡

የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ሩጫ አምባሳደር እና የጥንድ የኦሊምፒክ 5000ሜ ሻምፒዮኗ መሰረት ደፋር በእሁዱ ውድድር ወቅት ስትናገር ‹‹ይህ ውድድር ሁሌም የተለየ ነው፡፡ በሁሉም የማህበረሰቡ ክፍሎች ወስጥ የሚገኙ ሴቶችን ስኬቶች ለማክበር እና ለሌሎቾ ሴቶች ስኬታማ የመሆን በራስ መተማመንን ለመስጠት አስደናቂ መድረክ ነው፡፡ ሁሌም በየዓመቱ እኛን ሴቶችን ማነሳሳት አይሳነውም›› ብላለች፡፡

ባንክ ኦፍ አሜሪካ አዲስ እና ጠለቅ ያለ የደንበኛ ግንኙነትን የመፍጠር፣ የቡድን አጋሮችን የማሳተፍ እና በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዘላቂ የኢኮኖሚ ተፅዕኖን የማገዝ እንቅስቃሴው አካል አድርጎ በስፖርት ውስጥ ካሉ እጅግ ታዋቂ ብራንዶች ጋር በአጋርነት ይሰራል፡፡

ባንክ ኦፍ አሜሪካ ዓለምአቀፋዊውን የብርታት መድረኩን በኢትዮጵያ ሁለቱም ውድድሮች – በአፍሪካ ትልቁ የጎዳና ሩጫ በሆነው የኖቬምበሩ ዓለምአቀፍ የ10ኪ.ሜ. እና የመጋቢቱ የቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. – ላይ ከሚወዳደሩ የቀጣይ ትውልድ ሯጮች ጋር በማስተሳሰር ስፖርት እንዴት ዕድሎችን ሊፈጥር እንደሚችል እና ሰዎች እና ማህበረሰቦችን እንደሚያዋህድ ማሳየቱን ቀጥሏል፡፡

ባንክ ኦፍ አሜሪካ ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር ካለው አጋርነት ባሻገር በሩጫ፣ እግር ኳስ እና ጎልፍ ከዓለም አቀፍ ብራንዶች እና ሁነቶች ጋር በአጋርነት ይሰራል፡፡ እነዚህም Boston Marathon presented by Bank of America፣ Bank of America Chicago Marathon እና Chicago Distance Series፣ የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ፣ የአሜሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ሁሉም 27 የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድኖች እንዲሁም በጎልፍ የማስተርስ ውድድር እና Augusta National Women’s Amateur ናቸው፡፡

via Great Ethiopian Run

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

 Three-time Olympic gold medalist Gabby Thomas has arrived in the Ethiopian capital ahead of the highly anticipated Addis Ababa Grand Prix. Her arrival marks a significant milestone for the region,…

You Missed

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

Saint George respond on the pitch 

Saint George respond on the pitch