አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ የ2.8 ሚሊዮን ብር እና 40 ግራም የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበረከተላት።

(ስፖርት ኮሚሽን)

በቶኪዮ 2020 ፖራሊምፒክ ጨዋታ በ1500 ሜትር T-13 አይነስውራን ጭላንጭል ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስመዘገበችው አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ የ2.8 ሚሊዮን ብር እና 40 ግራም የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል ።

አትሌት ትዕግሥት ገዛኸኝ 04:23:24 በሆነ ሰዓት በመግባት ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ በማስመዝገብ በፖራሊምፒክ ጨዋታ ታሪክ መስራቷ ይታወሳል ።

የቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ንጋቱ ኃ/ማሪያም 400 ሺህ ብር ሲሸለም ፤

በ1500 ሜትር እጅ ጉዳት T-46 5ኛ ደረጃን በመያዝ ዲፕሎማ ያስመዘገበው አትሌት ገመቹ አመኑ የ200ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

በተመሳሳይ በ1500 ሜትር አይነስውራን ጭላንጭል T-13 7ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው አትሌት ታምሩ ከፍያለው 150 ሺህ ብር ተሸልሟል ።

የቡድኑ ሀኪም 100 ሺህ ብር ተሸልሟል ።

በቶኪዮ 2020 ፖራሊምፒክ ጨዋታ ኢትዮጵያ በ 3 አትሌቶች የተወከለች ሲሆን 1 ወርቅ ሁለት ዲፕሎማ በማግኘት ከዓለም 59ኛ ከአፍሪካ 6ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች ።

  • Related Posts

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Decorated two-time former World champion and Olympic medallist, Gudaf Tsegay, has been banned for four months by the Athletics Integrity Unit (AIU) under a Case Resolution Agreement, after admitting to…

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    The Ethiopia national under-17 football team will face Mozambique national under-17 football team in a play-off match that will determine qualification for the FIFA U-17 World Cup. Ethiopia defeated Tunisia…

    Leave a Reply

    You Missed

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

    Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

    CBE Crowned Women’s Premier League Champions

    CBE Crowned Women’s Premier League Champions

    Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

    Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች