በታላላቆቹ የአውሮፓ ሊጎች ግቦችን እያመረቱ ያሉ አምስት ተጫዋቾች

በዘንድሮው የውድድር ዘመን በአምስቱ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ከዚህ በፊት በግብ አስቆጣሪነታቸው የሚታወቁት ተጫዋቾች አሁንም ግብ ማምረታቸውን ቀጥለውበታል፡፡ እንደሀሪ ኬን ፤ አርሊንግ ሀላንድ እና ኪሊያን ምባፔ ያሉ ተጫዋቾች በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ግንባር ቀደም ናቸው፡፡

እንደስፖርቲንግ ፔዲያ ዘገባ ከሆነ ደግሞ የሞናኮው የፊት መስመር ተጫዋች አንሱ ፋቲ በወጥነት እንደዚሁም እድሎችን በመጠቀም አንጻር በአውሮፓ ያሉትን ታላላቅ አጥቂዎች እንደሚበልጣቸው ቁጥራዊ መረጃዎችን አስደግፎ አቅርቧል፡፡

አንሱ ፋቲ በተሰለፈባቸው ሁሉም የሞናኮ ጨዋታዎች ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡ በ3 የሊግ ጨዋታዎች 5 ግቦች አሉት፡፡  ይህም በየ32 ደቂቃው ግቦችን እንደሚያስቆጥር ማሳያ ነው፡፡ ፋቲ ምንም እንኳን ለረጅም ጊዜ በጉዳት ርቆ የቆየ ቢሆንም ወዲያውኑ ወደግብ ማግባቱ መመለስ ችሏል፡፡ እንደአንሱ ፋቲ በተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሁሉ ግብ ማስቆጠር የቻለው ሀሪ ኬን ሲሆን በየ45 ደቂቃው ግብ እንደሚያስቆጥር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሀላንድ ግቦችን በየ66 ደቂቃ የሚያስቆጥር ሲሆን ምባፔ በበኩሉ በየ72 ደቂቃው ግቦችን ያስቆጥራል፡፡

የአይንትራክት ፍራንክፈርቱ ወጣት ተጫዋች ካን ኡዙን በተሰለፈባቸው 80% ጨዋታዎች ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡

ሀላንድን የሚጠጋ ሪከርድ በፕሪሚየር ሊጉ ያለው የቦርንማውዙ አጥቂ አንትዎን ሴሜንዮ ሲሆን በተሰለፈባቸው 57% ጨዋታዎች ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

Brook Genene

Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

Related Posts

ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

የቀድሞው የቼልሲ የመሀል ተከላካይ ጆን ቴሪ ጥር ላይ በተሰናበቱት አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ ምትክ የጊዜያዊ አሰልጣኝነት እድል ባለማግኘቱ ደስተኛ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡  ጆን ቴሪ በቼልሲ አካዳሚ በበጎ ፈቃድ አሰልጣኝነት በወር ሁለት ቀን…

ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

በበረከት ጸጋዬ ሞሮኮ የ AFCON 2025 ን በስድስት አስተናጋጅ ከተሞች ውስጥ ባሉ ዘጠኝ ስታዲየሞች እያስተናገደች ነው፣ ይህም የአገሪቱንዘመናዊ እና የተለያየ የእግር ኳስ መሠረተ ልማት አጉልቶ ያሳያል። ቀጣዩ አጭር ዳሰሳ ለውድድሩ…

You Missed

Ethiopia Bunna appoints new chairman 

Ethiopia Bunna appoints new chairman 

Diribe Welteji banned for two years

Diribe Welteji banned for two years

ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ