25ኛ ዓመት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ህዳር 14 / 2018 ዓ.ም. ይካሔዳል

  • News
  • April 25, 2025
  • 0 Comments

የብር ኢዮቤልዩ ላይ የደረሰው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ሊከናወን ሰባት ወራት ቀሩት። ህዳር 16 ቀን 1994ዓ.ም. ጅማሮውን ያደረገው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በቀጣይ ህዳር 14 ቀን 2018ዓ.ም. 25ኛ ዙር ውድድሩን ያከናውናል።

ከአፍሪካ ትልቁ የ10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ውድድር የሆነው ዝግጅቱ ባለፉት 24 የውድድር ዓመታት ወደ 760ሺህ አካባቢ ሰው በ10ኪ.ሜ. ውድድሩ ላይ አሳትፏል።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የዘንድሮ ውድድር በተጠናቀቀ ማግስት የ25ኛ ዓመት ክብረበዓሉን አስመልክቶ ለቀጣዩ ዓመት 500 ቀዳሚ ተሳታፊዎች በነጻ ምዝገባ ያከናወነ መሆኑ ይታወሳል። ለሌሎች የውድድሩ ተሳታፊዎች ምዝገባ ሐምሌ ወር ላይ እንደሚከናወን ተገልጿል።

“25ኛ ዓመታችንን አብረውን በመሆን ካበረቱን ሁሉ ጋር ለማክበር ተዘጋጅተናል ፤ ደስታችንን ከራሳችን ለመጀመር በዚህ እሁድ ኬንያ በሚደረገው ኤልዶሬት ማራቶን ላይ ተሳትፈን እና ሩጫችንን አስተዋውቀን እንመለሳለን።” ያሉት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ “ከወዲሁ ከሩጫችን ጋር የተያያዙ የተሳታፊዎቻችንን ልዩ ልዩ ታሪኮች እና ገጠመኞች መሰብሰብ ስለጀመርን በማህበራዊ ሚድያ ገጾቻችን ላይ ቢነገር የሚሉትን ትውስታቸውን ያካፍሉን” ሲሉ ለተሳታፊዎች ጥሪ አቅርበዋል።

ከ24 ዓመታት በፊት ውድድሩ ሲጀመር ኃይሌ ገብረስላሴ እና ብርሃኔ አደሬ የመጀመሪያውን ዓመት ውድድር ያሸነፉ አትሌቶች ሲሆኑ ፤ በዘንድሮ ውድድር ላይ ወጣቶቹ አትሌቶች ቢንያም መሃሪ እና አሳየች አይቸው ማሸነፋቸው ይታወሳል።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተሳታፊዎች ትዝታዎቻቸውን በ communications@ethiopianrun.org ላይ ማጋራት እንደሚችሉ ገልጿል።

  • Girmachew Kebede

    Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

    Related Posts

    Diribe Welteji banned for two years

    The Court of Arbitration for Sport (CAS) has partially upheld an appeal by World Athletics against the Ethiopian National Anti-Doping Office (ETH-NADO) and middle-distance runner Diribe Welteji Kejelcha (Ethiopia). Ms…

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    የቀድሞው የቼልሲ የመሀል ተከላካይ ጆን ቴሪ ጥር ላይ በተሰናበቱት አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ ምትክ የጊዜያዊ አሰልጣኝነት እድል ባለማግኘቱ ደስተኛ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡  ጆን ቴሪ በቼልሲ አካዳሚ በበጎ ፈቃድ አሰልጣኝነት በወር ሁለት ቀን…

    You Missed

    Ethiopia Bunna appoints new chairman 

    Ethiopia Bunna appoints new chairman 

    Diribe Welteji banned for two years

    Diribe Welteji banned for two years

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

    ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

    ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ