ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ህዳር 14 ቀን በሚደረገው የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ላይ ለሚያሸንፉ አትሌቶች በድምሩ ከ1.8ሚሊዮን ብር በላይ ሊሸልም ነው።

ከ2017 ዓ.ም. ጀምሮ የአለም አትሌቲክስ (Label Road Race) ደረጃ የተሰጠው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ሃያ አምስተኛ ዓመት ውድድሩን በማስመልከት በአንደኛነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሚያበረክተውን የገንዘብ ሽልማት ወደ አራት መቶ ሺህ (400,000) ብር ከፍ አድርጓል።

በዚህም መሰረት ሽልማቱ በውድድሩ ላይ ባለፈው አመት ለአሸናፊዎች በሽልማትነት ተበርክቶ ከነበረው 250ሺህ ብር በስልሳ በመቶ (60%) አድጓል። በተመሳሳይ ሁለተኛ ለሚሆኑ የ200ሺህ አንዲሁም ሶስተኛ ሆነው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የ100ሺህ ብር ሽልማት አንደሚበረከት ይፋ ተደርጓል።

የውድድሩን ጥራት አና የአትሌቶችን ፉክክር ከፍ ማድረግ አንዲቻልም በክለብ አና የስፖርት ማኔጅመንት ውስጥ ከሚገኙ አትሌቶች በተጨማሪ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች ዕድል ለመፍጠር ቅዳሜ ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም. በእንጦጦ ፓርክ የማጣሪያ ውድድር ይካሔዳል። ይህም ማጣሪያ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች በውድድሩ ላይ የመሳተፍ ዕድልን ይፈጥርላቸዋል።

ቅዳሜ ከአትሌቶች የማጣሪያ ውድድር በተጨማሪም 9ኛው ዙር የወርሃዊው እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ ባለፉት ውድድሮች ላይ ሰባት እና ከዛ በላይ ለሆነ ጊዜ የሮጡ ተሳታፊዎች ልዩ ሽልማት ይበረከትላቸዋል።

(ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ)

Girmachew Kebede

Related Posts

St. George wins the City Cup 

Ethiopia’s oldest and most successful club St. George have added another trophy to their cabinet by winning the 19th edition of the Addis Ababa City Cup. This is the club’s…

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

© Getty Images ኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ፈይሳ በባንክ ኦፍ አሜሪካ ቺካጎ ማራቶን ባለድል ሆናለች። መገርቱ አለሙ ደግሞ በሁለተኛነት አጠናቅቃለች። ሐዊ ውድድሩን ያሸነፈችበት ጊዜ 2:14:56 ሲሆን የግሏ ምርጥ ሰዓት ነው።  የዓለም ማራቶን ሜጀር…

You Missed

St. George wins the City Cup 

St. George wins the City Cup 

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ

የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ