Girmachew Kebede
የካፍ ከ15 ዓመት በታች የአፍሪካ ትምህርት ቤቶች እግር ኳስ ሻምፕዮና የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ማጣሪያ ኢትዮጵያ በፍፃሜው ትፋለማለች።
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሦስተኛ ቀን ውሎውን በመጨረሻ የምድብ እና የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ሲደረጉ ኢትዮጵያ በሁለቱም ጾታ ጨዋታዎቹን በድል ተወጥታለች።
በወንዶች የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ኢትዮጵያ ከ ቡሩንዲ መደበኛውን ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ አጠናቀው በመለያ ምቶች ኢትዮጵያ 14-13 በማሸነፍ ወደ ፍጻሜ ስታልፍ አስተናጋጇ ዩጋንዳን በፍጻሜው የምትገጥም ይሆናል። በዚህ ጨዋታ በድምሩ 30 የመለያ ምቶች ተመትተዋል።
በሴቶች አስተናጋጇ ዩጋንዳን የገጠመችው ኢትዮጵያ መደበኛውን ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በማጠናቀቅ በመለያ ምቶች 3-2 አሸንፋለች። በፍጻሜውም ከታንዛንያ ጋር ትፋለማለች።
Girmachew Kebede
Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.