የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

ከኬንያ አንጋፋ የረጅም ርቀት ሩጫ አትሌቶች መካከል ሦስቱ – ፖል ቴርጋት፣ ዳንኤል ኮመን እና ሞሰስ ታኑይ – እሁድ ህዳር 14 ቀን 2018 በሚካሄደው የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ 10 ኪሎ ሜትር ላይ ለመገኘት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተገለፀ።

ሦስቱም አትሌቶች በዓለም አቀፍ የሩጫ ሕይወታቸው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን በ1994ዓ.ም. ከመሠረተውና የኢትዮጵያ የረዥም ርቀት ሩጫ ምልክት የሆነው ኃይሌ ገብረሥላሴ ዋና ተፎካካሪ ነበሩ።

ቴርጋት ቀደም ሲል እ.ኤ.አ. በመስከረም ወር 2003 በበርሊን የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰን ከሰበረ በኋላ በውድድሩ ላይ በእንግድነት ተገኝቶ ነበር። በ1990ዎቹ ከኢትዮጵያዊው ጓደኛው ኃይሌ ጋር ከፍተኛ ፉክክር የነበረው ሲሆን ፤ በ1996 እና በ2000 ኦሎምፒክ ኃይሌን በመከተል የብር ሜዳሊያውዎችን አግኝቷል። ሁለቱም ወደ ማራቶን ሲያድጉም ፉክክሩ የቀጠለ ሲሆን፣ ኃይሌ በሴፕቴምበር 2007 በመጀመሪያው የማራቶን ክብረ ወሰን የዓለም ሪከርዱን ከቴርጋት በ29 ሰከንድ ልዩነት ወስዷል።

ዳንኤል ኮመንም ከ1996 እስከ 1998 ባሉት ሦስት ዓመታት በትራክ ላይ ከኃይሌ ገብረሥላሴ ጋር ከባድ ፉክክር ነበረው።

እ.ኤ.አ. 1996 በተካሔደው የአትላንታ ኦሎምፒክ ቡድን ውስጥ ያልተካተተው ኮመን በሴፕቴምበር 1 ቀን 1996 በጣሊያኗ ሪየቲ የ3000 ሜትርን 7፡20.67 በመሮጥ የዓለም ክብረ ወሰንን ይዞ ነበር ፤ ይህም ጃኮብ ኢንገብሪግስተን በኦገስት 2024 እስኪሰብረው ድረስ ለ28 ዓመታት ያህል ዘልቋል። በ1997 ኮመን የ5000ሜትር የዓለም ክብረ ወሰንን 12፡39.74 በመሮጥ ከኃይሌ ወስዶ የነበረ ቢሆንም ኃይሌ በ12፡39.36 በመሮጥ በአንድ ዓመት ውስጥ መልሶ ወስዶታል።

ሞሰስ ታኑይ በዚህ ወር መጨረሻ ወደ አዲስ አበባ ሲመጣ ለሦስተኛ ተከታታይ ጊዜው ነው። ታኑይ የሁለት የዓለም ሻምፒዮና አሸናፊ (በ1991 በትራክ እና በ1995 በጎዳና ላይ) ሲሆን ፤ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአጋርነት የሚሰራው የኤልዶሬት ማራቶን የውድድር ዳይሬክተር ነው። ታኑይ በ1993 የዓለም ሻምፒዮና የ10,000ሜትር ውድድር ላይ ከኃይሌ ገብረሥላሴ ጋር አይረሴ ፉክክር ቢያደርግም በመጨረሻው ዙር ጫማው በመውለቁ ኃይሌ አሸንፎት እንደነበር ይታወሳል።

ሶስቱም የኬንያ ታላላቅ አትሌቶች ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ በእንግድነት ታድመውበት በነበረው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መድረክ ላይ በድጋሚ ከኃይሌ እና ከሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ጋር መገኘት የ25ኛውን ዓመት ክብረ በዓል በሚያደምቁት 55,000 ተሳታፊዎች ላይ ተጨማሪ ደስታን ይፈጥራል።

የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ 10 ኪሎ ሜትር መነሻዎቹን መስቀል አደባባይ እና ግዮን ሆቴል በማድረግ ፤ እሁድ ህዳር 14 ቀን 2018ዓ.ም. ይካሔዳል።

(ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ)

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

የጀርመን ብሄራዊ ቡድን የ2014ቱን የአለም ዋንጫ ካሸነፉ ማግስት አንድ ከባድ ነገርን መጋፈጥ ነበረባቸው:: ኑሮ ያለድንቁ አጥቂ ሚሮስላቭ ክሎዘ! በአሁኑ ሰአት በጀርመን ሁለተኛ ዲቪዚዮን የቡንደስሊጋ ዋንጫን ብዙ ጊዜ በማሸነፍ ሁለተኛ ላይ…

CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

This year’s edition of the CECAFA U-17 tournament will officially kick off on Saturday in Ethiopia. Ten countries will take part in the competition the list of which includes hosts…

You Missed

ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

ኒኮ ዋልተማደ- በወሳኝ ሰአት የተገኘ አጥቂ

CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

CECAFA U-17 tournament to start on Saturday

Chelsea Fans Can’t Connect With Squad, But Maresca Needs Time

Chelsea Fans Can’t Connect With Squad, But Maresca Needs Time

የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

የኃይሌ ተፎካካሪዎች በታላቁ ሩጫ. . .

“ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

“ ኳስ ማቀበል አርት እንደሆነ ከጄራርድ እና አሎንሶ ተምሬአለሁ” ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ

Wanda Diamond League season calendar confirmed for 2026

Wanda Diamond League season calendar confirmed for 2026