ለኤሊት የጨዋታ አመራሮች የኢንተርናሽናል ዳኝነት ደረጃ ፈተና ተሰጠ

  • News
  • September 17, 2021
  • 0 Comments

(እግር ኳስ ፌዴሬሽን)

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ልማትና አስተዳዳር ዳይሬክቶሬት ከዳኞች ልማት ኮሚቴ ጋር በመቀናጀት በ2022 የውድድር ዘመን በኢንተርናሽናል ደረጃ እግር ኳስን መምራት የሚችሉ ዳኞችን ለመለየት ለ12 ኤሊት ወንዶችና ሴቶች የጨዋታ አመራሮች/ ዳኞች/ ትናንት መስከረም 6 ቀን 2014 ዓ.ም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት የጽሑፍ፣ የቃልና የኮምፒውተር ክህሎት ፈተና አካሄደ፡፡

ፈተናው መስከረም 5 ቀን 2014 ዓ.ም በተደረገው የኢንተርናሽናል እና የኤሊት የጨዋታ አመራሮች የአካል ብቃት ፈተና ውጤት ማለፋቸውን ለአረጋገጡ 12 ኤሊት ዳኞች የተሰጠ ሲሆን ከነዚህም አንድ ሴት ዋና ዳኛ ፣ ከወንዶች 7 ዋና እና 4 ረዳት ዳኞች ይገኙበታል፡፡


ለኤሊት ዳኞች የተዘጋጀው ፈተና ዓላማ ቀደም ሲል በኢንተርናሽናል ደረጃ የነበሩት ዋና እና ረዳት ዳኞች ቁጥር በተለያዩ ምክንያት በመቀነሱ እነሱን ለመተካት የተዘጋጀ ሲሆን በመመዘኛ ፈተናዎቹ እና በቀረበው መስፈርት መሰረት የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ኤሊት ዳኞችን ወደ ኢንተርናሽናል የጨዋታ አመራር ደረጃ ብቃት በመመዘን ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው፡፡


በኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2021 በዓለም አቀፋ እግር ኳስ ማህበር /ፊፋ/ ኮታ መሠረት በዋና ዳኝነት 7 ወንድ እና 4 ሴት፣ በረዳት ዳኝነት በተመሳሳይ 7 ወንድ እና 4 ሴት በአጠቃላይ 11 ኢንተርናሽናል ዋና እና 11 ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኞች ተመዝግበው ባጅ ከወሰዱት መካከል 4 ዳኞች በተለያዩ ምክንያቶች በመቀነሳቸው እነዚህን ለመተካት በተዘጋጀው የኤሊቶች ፈተና የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ 4 ዳኞች ( አንድ /1/ ሴት ዋና ዳኛ እንዲሁም 2 ዋና 1 ረዳት ወንዶች) ዳኞች ለ2022 በኢንተርናሽናል ዳኝነት ዝርዝር ውስጥ የሚካተቱ ይሆናል፡፡

Girmachew Kebede

Related Posts

St. George wins the City Cup 

Ethiopia’s oldest and most successful club St. George have added another trophy to their cabinet by winning the 19th edition of the Addis Ababa City Cup. This is the club’s…

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

© Getty Images ኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ፈይሳ በባንክ ኦፍ አሜሪካ ቺካጎ ማራቶን ባለድል ሆናለች። መገርቱ አለሙ ደግሞ በሁለተኛነት አጠናቅቃለች። ሐዊ ውድድሩን ያሸነፈችበት ጊዜ 2:14:56 ሲሆን የግሏ ምርጥ ሰዓት ነው።  የዓለም ማራቶን ሜጀር…

Leave a Reply

You Missed

St. George wins the City Cup 

St. George wins the City Cup 

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

ሐዊ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች

Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

Great Ethiopian Run Winners to Receive Record Prize Money

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

Ethiopia’s Shure Demise Seeks Third Victory at TCS Toronto Waterfront Marathon

የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ

የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ