ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡
ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን አሸናፊዋን ጆይሲሊን ጄፖሴኪ በማስከተል ነው ውድድሩን ማሸነፍ የቻለችው፡፡
“ የራሴን ክብረወሰን በማሻሻሌ እና በድጋሚ በለንደን በማሸነፌ ደስተኛ ነኝ” በማለት ትዕግስት ከውድድሩ በኋላ ተናግራለች፡፡ “ ለስኬቴ የተለየ ሚስጥር የለም፡፡ ጠንክሬ ሰርቻለሁ በዛም ምክንያት ማሸነፍ ችያለሁ” በማለት አክላለች፡፡
የዚህ አመት ውድድር ከሌላው ጊዜ በተለየ ጠንካራ እንደነበር እና ከሄለን እና ጆይሲሊን ከባድ ፉክክር እንደገጠማት ትዕግስት ገልጻለች፡፡



