አስተያየት፡ አጨዋወቱ ኖሮ ተጫዋቾች ሳይኖሩ እንዳይቀሩ

ሰሞኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የብሔራዊ ቡድኖቻችንን አጨዋወት ለመወሰን ከአሰልጣኞቻችን ጋር ሊመክር ነበር። ጥሩ ጅምር ይመስለኛል። ሆኖም ከዶሮዋና ከእንቁላሏ አይነት ክርክር ውስጥ መግባት ባልፈልግም ፌዴሬሽኑ ጊዜውን በቅድሚያ የሚሰጠው የተጫዋቾች ልማት ላይ ቢሆን እመርጣለሁ።

ጥያቄዎቹም

ተጫዋቾች ከየት እናገኛለን?…እንዴት እናሳድጋቸዋለን?…የት እናሳድጋቸዋለን?…እንዴት እናሰለጥናቸዋለን?

እንዴት ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች እናደርጋቸዋለን? መሆን አለባቸው።

እነዚህን ጥያቄዎች በትክክል ከመለስን በኋላ የትኛውንም አይነት የጨዋታ መንገድ ይኑረን ለስኬት ቅርብ እንሆናለን ብዬ አምናለሁ።

ለምሳሌ ፈረንሳይ አንድ የብሔራዊ ቡድን አጨዋወት መንገድ ያላት አይመስለኝም። ሆኖም ግልፅ የሆነ የተጫዋቾች ልማት ሞዴል አላት። በዚህም ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት አራት ጊዜ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ደርሳለች። ሁለት ዋንጫ አንስታለች። ሁለቱን ፍፃሜዎች የተሽነፈችውም በመለያ ምት ብቻ ነበር።

በብሔራዊ ቡድኖቿ አጨዋወት የምትታወቀው ስፔንም በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ጭምር የተመሰከረለት ከgrassroot የሚጀምር የወጣቶች ልማት ሞዴል አላት።

የጀርመን እግር ኳስ ለውጥ መነሻም ፌዴሬሽኑን፣ የአውራጃ ፌዴሬሽኖችን፣ ትምህርት ቤቶችን እና ክለቦችን ያሳተፈ የወጣቶች ተሰጥኦ ልማት ነው። ምናልባት እነዚህ የአውሮፓ ሀገራት የቀደመ የእግር ኳስ ታሪክ ያላቸው ናቸው ካልን እስኪ የኳስ የስኬት ታሪክ የሌላትን ኡዝቤኪስታንን እንመልከት።

ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫ የምትሳተፈው ኡዝቤኪስታን አሁን ማንቸስተር ሲቲ የሚጫወተውን ኩዛኖቭን አይነት ተጫዋቾች ማፍራት የቻለችው ከሰባት ዓመት በፊት “ሰበብ ይብቃኝ” ብላ በጀመረችው የተጫዋቾች ልማት ነው። በወቅቱ በፕሬዚደንታዊ አዋጅ የአምስት ዓመት የተጫዋቾች ልማት ዕቅድ አወጣች። በ14ቱም ክልሎቿ የህፃናት እና ወጣቶች አካዳሚዎችን ገነባች። የስልጠና እና የውድድር ጥራትን በእጅጉ አሻሻለች። ከዚህ በኃላ በተከታታይ የእግር ኳስ ልማትን የሚመለከቱ ህጎችን አውጥታለች። በዚህም ከሁለት ዓመት በፊት የኤዥያ ከ20 ዓመት በታች ዋንጫን አሸነፈች። ከ23 ዓመት በታች ቡድኗ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦሊምፒክ ተሳተፈ። ከ17 ዓመት በታች ቡድኗ ለመጀመሪያ ጊዜ የአህጉሩ ሻምፒዮን ሆነ። ዋናው ብሔራዊ ቡድኗም ለመጀመሪያ ጊዜ ለዓለም ዋንጫ አለፈ። በመህል ኩዛኖቭ በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የተጫወተ የመጀመሪያው የሀገሪቱ ዜጋ ሆነ። ግልፅ የእግር ኳስ እና የተጫዋቾች ልማት ስኬት ይህ ነው።

የብሔራዊ ቡድን አጨዋወት መኖር ጥሩ ነው። አጨዋወቱ ያለ ተጨዋቾች ግን ምንም ነው። ዋናው ትኩረትም በርካታ ጥራት ያላቸው ተጫዋቾችን ማፍራት ላይ መሆን አለበት።

  • Girmachew Kebede

    Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

    Related Posts

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች የ4 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ‘ሌሎችን ለመርዳት እሮጣለሁ’ በተሰኘው የ2018 ሶፊማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለምአቀፍ 10ኪ.ሜ. የበጎ አድራጎት ዘመቻው አማካኝነት ያሰባሰበውን 4 ሚሊዮን ብር በቼሻየር ኢትዮጵያ መናገሻ ቢሮ በተከናወነ ደማቅ ስነ-ስርዓት ለተመረጡ…

    You Missed

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    Saint George respond on the pitch 

    Saint George respond on the pitch