ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ህዳር 14 ቀን በሚደረገው የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ላይ ለሚያሸንፉ አትሌቶች በድምሩ ከ1.8ሚሊዮን ብር በላይ ሊሸልም ነው።

ከ2017 ዓ.ም. ጀምሮ የአለም አትሌቲክስ (Label Road Race) ደረጃ የተሰጠው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ሃያ አምስተኛ ዓመት ውድድሩን በማስመልከት በአንደኛነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሚያበረክተውን የገንዘብ ሽልማት ወደ አራት መቶ ሺህ (400,000) ብር ከፍ አድርጓል።

በዚህም መሰረት ሽልማቱ በውድድሩ ላይ ባለፈው አመት ለአሸናፊዎች በሽልማትነት ተበርክቶ ከነበረው 250ሺህ ብር በስልሳ በመቶ (60%) አድጓል። በተመሳሳይ ሁለተኛ ለሚሆኑ የ200ሺህ አንዲሁም ሶስተኛ ሆነው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የ100ሺህ ብር ሽልማት አንደሚበረከት ይፋ ተደርጓል።

የውድድሩን ጥራት አና የአትሌቶችን ፉክክር ከፍ ማድረግ አንዲቻልም በክለብ አና የስፖርት ማኔጅመንት ውስጥ ከሚገኙ አትሌቶች በተጨማሪ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች ዕድል ለመፍጠር ቅዳሜ ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም. በእንጦጦ ፓርክ የማጣሪያ ውድድር ይካሔዳል። ይህም ማጣሪያ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች በውድድሩ ላይ የመሳተፍ ዕድልን ይፈጥርላቸዋል።

ቅዳሜ ከአትሌቶች የማጣሪያ ውድድር በተጨማሪም 9ኛው ዙር የወርሃዊው እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ ባለፉት ውድድሮች ላይ ሰባት እና ከዛ በላይ ለሆነ ጊዜ የሮጡ ተሳታፊዎች ልዩ ሽልማት ይበረከትላቸዋል።

(ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ)

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

Diribe Welteji banned for two years

The Court of Arbitration for Sport (CAS) has partially upheld an appeal by World Athletics against the Ethiopian National Anti-Doping Office (ETH-NADO) and middle-distance runner Diribe Welteji Kejelcha (Ethiopia). Ms…

ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

የቀድሞው የቼልሲ የመሀል ተከላካይ ጆን ቴሪ ጥር ላይ በተሰናበቱት አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ ምትክ የጊዜያዊ አሰልጣኝነት እድል ባለማግኘቱ ደስተኛ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡  ጆን ቴሪ በቼልሲ አካዳሚ በበጎ ፈቃድ አሰልጣኝነት በወር ሁለት ቀን…

You Missed

Ethiopia Bunna appoints new chairman 

Ethiopia Bunna appoints new chairman 

Diribe Welteji banned for two years

Diribe Welteji banned for two years

ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ