የአትላስ አናብስት አለምን አስደምመዋል

AL RAYYAN, QATAR – DECEMBER 06: Jawad El Yamiq of Morocco celebrates victory after extra time and penalties during the FIFA World Cup Qatar 2022 Round of 16 match between Morocco and Spain at Education City Stadium on December 06, 2022 in Al Rayyan, Qatar. (Photo by Clive Brunskill/Getty Images)

መቶ ሃያ ደቂቃዎችን ከፈጀ እልህ አስጨራሽ ፍልሚያ መልስ የአፍሪካ ተወካይ የሆነችው ሞሮኮ ስፔንን በመለያ ምት 3-0 በመርታት የሩብ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ችላለች፡፡ ይህም ከካሜሩን፤ሴኔጋል እና ጋና በመቀጠል የአለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜን የተቀላቀለች አራተኛዋ አፍሪካዊት ሀገር አድርጓታል፡፡

ሁሉም ተጫዋች ድንቅ እንቅስቃሴን አሳይቷል በማለት ከጫወታው በኋላ አስተያየቱን የሰጠው ግብ ጠባቂው ያሲን ቦኖ ከተመቱበት ሶስት የፍጹም ቅጣት ምቶች ሁለቱን በማዳን የጫወታው ኮከብ መሆን ችሏል ( ሌላኛዋ ፍጹም ቅጣት ምት በግቡ ቋሚ ተመልሳለች)፡፡

በጫወታው ስፔኖች እንደተለመደው እና እንደተጠበቀው የኳስ ቁጥጥር ብልጫን መያዝ ቢችሉም ከአንድ ኢላማውን ከጠበቀ ሙከራ ውጪ ቦኖን መረበሽ አልቻሉም፡፡ የጫወታው ምርጥ ዕድል የተገኘው 120 ደቂቃ ሊጠናቀቅ ሲል በሳራቢያ በኩል ነበር፡፡ እንዳመከነው ፍጽም ቅጣት ምት ሁሉ የግቡ ቋሚ መልሶበታል፡፡

ድሉ ሙሉ አፍሪካውያንን ያስፈነደቀ እና ሞሮኮአዊያንን ደግሞ ያኮራ ሆኗል፡፡ ከጫወታው በኋላ በውጤቱ የተደሰተው አንድ የሞሮኮ ጋዜጠኛ “ ጥያቄ የለኝም፡፡ ነገር ግን ቦኖ እና አሰልጣኝ ዋሊድን አመሰግናለሁ፡፡ የ40 ሚሊየን የሞሮኮ ህዝቦችን እምነት ቦኖ አግኝተሃል“ በማለት እንባ ተናንቆት ተናግሯል፡፡

ሶፊያን አምራባት ከጉዳት ጋር እየተገለ የመሃል ሜዳውን ፍልሚያ በተወጣበት ፤ ዋሊድ ቸዲራ ከአንድም ሁለት ወርቃማ ዕድሎችን ባልተጠቀመበት፤ ሮማን ሳይስ ከእነጉዳቱ ጨዋታዉን በጨረሰበት እና ሶፊያን ቡፋል ለሎሬንቴ ጭንቀት ሆኖ ባመሸበት ጨዋታ የፒኤስጂው የቀኝ መስመር ተከላካይ አሽራፍ ሃኪሚ ተወልዶ ያደገባትን ሀገር በቄንጠኛ ፍጹም ቅጣት ምት ከውድድሩ አሰናብቷታል፡፡

ሰርጂዮ ቡሽኬትስ እድለቢስ እንደሆኑ እና ሁልጊዜም በፍጹም ቅጣት ምት የሚያልቅ ጨዋታ ውጤቱ እንደማይታወቅ ገልጻል፡፡ የቡድኑ አሰልጣኝ ሉዊስ ሄነሪኬ በበኩላቸው ቡድናቸው 11 ሙከራዎችን ሞክሮ አንድ ብቻ ኢላማውን የጠበቀ እንደነበር ሲያስታውሱ በቡድናቸው እንደኮሩ እና የፍጹም ቅጣት መቺዎቹን የመረጡት እራሳቸው ስለሆኑ ኃላፊነትን እንደሚወስዱ ተናግረዋል፡፡

Pic via Morocco FA Twitter

በቀጣይ ሞሮኮ ከፖርቹጋል ጋር በሩብ ፍጻሜው የምትገናኝ ሲሆን ስዊዘርላንድን 6-1 ከቀጣችው ቡድን ቀላል ፈተና እንደማይጠብቃት መገመት ይቻላል፡፡ ሆኖም ግን ወደ ግማሽ ፍጻሜ በማለፍ ደማቅ ታሪክን የመጻፍ ትልቅ ዕድል አላት፡፡

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Decorated two-time former World champion and Olympic medallist, Gudaf Tsegay, has been banned for four months by the Athletics Integrity Unit (AIU) under a Case Resolution Agreement, after admitting to…

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    The Ethiopia national under-17 football team will face Mozambique national under-17 football team in a play-off match that will determine qualification for the FIFA U-17 World Cup. Ethiopia defeated Tunisia…

    Leave a Reply

    You Missed

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Gudaf Tsegay banned for four months

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

    Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

    Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

    CBE Crowned Women’s Premier League Champions

    CBE Crowned Women’s Premier League Champions

    Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

    Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች