የአፍሪካ ዋንጫ ተሳታፊ ብሄራዊ ቡድኖች አጭር ምልከታ ( ምድብ ሶስት)

በረከት ፀጋዬ

ምድብ ሶስት

ሞሮኮ፣ ጋና፣ ጋቦን፣ ኮሞሮስ 

ሞሮኮ

  • ተሳትፎ፡  18ኛ ጊዜ
  • ምርጥ ውጤት፡ ሻምፒዮን (1976)
  • አሰልጣኝ፡ ቫሂድ ሃሊልሆድዚች
  • ኮከብ ተጨዋች፡  አሽራፍ ሃኪሚ
ሃኪሚ ከክዋክብት ጋር የሚያሳያውን ብቃት በካሜሩን እንዲደግም ይጠበቃል

ምን ይጠብቃሉ፡ ከ2019 የአፍሪካ ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ስንበት መልስ ወደ አሰልጣኝነት ብቅ ያሉት ቦስኒያዊው ሃሊልሆድዚች ብዙ ለውጦችን ፈጥረዋል። ይህም አንጋፋ የነበረውን የቡድን ስብስብ በወጣቶች መቀየር የቻሉበት ይጠቀሳል። በዚ ሂደት ከቼልሲው የክንፍ አጥቂ ሃኪም ዚያች ጋር የፈጠሩት አለመግባባት ተጫዋቹን ወደ አፍሪካ ዋንጫ እንዳይጠራ አድርጎታል።  የዚህን ቁልፍ ተጫዋች በቀላሉ ተከላካዮችን የማለፍ ብቃትና ፍጥነት ማጣታቸው ዋጋ እንዳያስከፍላቸው ያሰጋል።

የአፍሪካን እግር ኳስ በደንብ የሚያውቁት ሃሊልሆድዚች በአህጉሪቱ ትልቅ የውድድር መድረክ ያላቸው አናሳ የውጤት ታሪክ ሌላው በአትላስ አንበሶቹ ላይ ጥያቄ የሚያጭር አጋጣሚ ነው። ምንም እንኳን ለዋንጫው ከሚታጩ ፊት አውራሪዎች ተርታ ባይመደቡም የመስመር ተከላካዩ አሽራፍ ሃኪሚ ወቅታዊ ምርጥ ብቃት ላይ መገኘት ግምቶችን ሊያፋልስ ይችላል። ከፔዤው ኮከብ በተጨማሪ የዎልቭሱ የመሃል ተከላካይ ሮማን ሳይስ፣ የባርሴሎናው አጥቂ አብዴ ኢዛላውዚሊ ለሞሮኮ ተጨማሪ ሃይልን የሚፈጥሩ ከዋክብቶች ናቸው። 

የ2019 አፍሪካ ዋንጫን ጨምሮ በመደበኛ 90 ደቂቃ ጨዋታ አንድም ሽንፈትን ያልቀመሱት ሞሮኮዎች በዚህኛው መድረክ ረጅም ርቀትን መጓዝ ያልማሉ። ምናልባትም ዋንጫውን ለማሸነፍ አቅም እንዳላቸው ጭምር ያስባሉ። ከጠንካራዋ የምድቡ ባላንጣቸው ጋና ጋር የሚያካሂዱት የመክፈቻ ጨዋታ ከወዲሁ የብዙዎችን ቀልብ የሚስብ ሆኖ እናገኘዋለን። ሌሎች የምድቡ ተፎካካሪዎቻቸው አቅም እዚ ግባ የማይባል መሆኑን በመጥቀስ ጋናና ሞሮኮ ከምድቡ ተያይዘው ያልፋሉ በማለት አቋሟሪዎች ግምታቸውን ያስቀምጣሉ። 

ጋና 

  • ተሳትፎ፡  23ኛ ጊዜ
  • ምርጥ ውጤት፡ ሻምፒዮን (1963፣65፣78፣82) 
  • አሰልጣኝ፡ ሚሎቫን ራጅቫክ
  • ኮከብ ተጨዋች፡ አንድሬ አየው
አየዉ የተቺዎቹን አፍ ለማዘጋት ከዚህ የተሻለ ጊዜ የሚያገኝ አይመስልም።

ምን ይጠብቃሉ፡ ከ1982 ወዲህ ዋንጫውን ከፍ ለማድረግ ባይታደሉም፤ ከጫፍ ደርሰው በሚያስቆጭ መልኩ ይሄን ክብር የተነጠቁበትን ሶስት አጋጣሚዎች መቀየር የጥቋቁር ኮከቦቹ ተቀዲሚ እቅድ ነው። ዳግም ብ/ቡድኑን ለማሰልጠን የተሾሙት ሚሎቫን ራጅቫክ ዋንጫውን የማሸነፍ የቤት ስራ ተሰጥቷቸው ካሜሩን ደርሰዋል። በ2010 አለም ዋንጫ እስከ ሩብ ፍፃሜ የተጓዘውን ቡድን የመሩት እኚሁ ሰርቢያዊ ከዛን ጊዜው ተጫዋቾቻቸው አንድሬ አየው እና ጆናታን ሜንሳህ ብቻ በአሁኑ ስብስብ ውስጥ ይገኛሉ። 

በዛው ዓመት በወጣቶች የተገነባ ቡድን ይዘው ለአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ቀርበው የነበረ ቢሆንም በግብፅ 1-0 ተሸንፈው ዋንጫውን አጥተዋል። ራጅቫክ ለወጣቶች ዕድልን በመስጠት አሸናፊ ቡድን መገንባትን ያቅዳሉ።  ለዚህም መቀመጫቸውን አውሮፓ ያደረጉ እንደ ካማልደን ሱሌማና (ሬንስ)፣ ኩዱስ ሞሃመድ (አያክስ)፣ ፊሊክስ አፊና ጂያን (ሮማ) እና ኤድመንድ አዶ (ሸሪፍ) የመሳሰሉ ወጣት ተስፈኞችን በቡድናቸው አካተዋል። ሌላው የ17 አመት ታዳጊ አቡዱል ፋቱ ኢሳሃኩ በጋና ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታው ያሳየው ብቃት አዲሱ አብዲ ፔሌ እስከ መባል ያደረሰው ሲሆን ይሄው ታዳጊ ሌላው የጋና ቁልፍ መሳሪያ በመሆን አፍሪካ ዋንጫውን እንደሚያደምቅ ተስፋ ተጥሎበታል። 

ተጥሎበታል።  ከእነዚህ ታዳጊዎች በተጨማሪ የአርሰናሉ አማካይ ቶማስ ፓርቴ፣ የፓላሱ የፊት አጥቂ ጆርዳን አየው እና የሌይስተሩ የኃላ ደጀን ዳንኤል አማርቴን ልምድ ከወጣቶቹ ጋር በማጣመር ዋንጫውን ማሸነፍ የራጅቫክ ተቀዳሚ እቅድ ይሆናል። ከግብፁ የአፍሪካ ዋንጫ በቱኒዝያ በጥሎ ማለፍ ተሸንፈው የወጡበትን አጋጣሚ ጋናውያን ደግመው መመልከት ፈፅሞ አይፈልጉም ሲል ጋናዊው ስፓርት ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሬድዋን አሳንቴ ለቢቢሲ አስተያየቱን ይሰጣል። 

ጋቦን 

  • ተሳትፎ፡  8ኛ ጊዜ
  • ምርጥ ውጤት፡ ሩብ ፍፃሜ (1996፣ 2012)
  • አሰልጣኝ፡ ፓትሪስ ኒቪው
  • ኮከብ ተጨዋች፡ ፔር ኤሜሪክ ኦውባሜያንግ
ኦውባሜያንግ በአርስናል የጠፋውን አቋሙን በጋቦን ማልያ ይፈልጋል

ምን ይጠብቃሉ፡ ጥቁር ግስላዎቹ በምድቡ ጠንካራ ተፎካካሪዎች በመኖራቸው ለማለፍ የሚኖራቸው ተስፋ ጥሩ ሶስተኛ በመሆን ላይ የተንጠለጠለ ሊሆን ይችላል። ለሃገሩ 29 ጎሎችን ያስቆጠረው ፔር ኤሜሪክ ኦውባሜያንግ አሁንም የቡድኑ ኮከብ ተጫዋች ነው። ከመክፈቻው ዋዜማ የተሰማው የኮከቡ አጥቂ በኮቪድ የመያዝ ዜና በቡድኑ የመክፈቻ ጨዋታዎች ላይ ጥላ እንዳያጠላ ያሰጋል።

ያሰጋል። ከኦውባሜያንግ በተጨማሪ ሌላው ወሳኝ የቡድኑ አማካይ ማሪዮ ሌሚና በኮቪድ የተያዘ ተጫዋች ሆኖ ራሱን አግልሏል። አምስተኛ የአፍሪካ ዋንጫውን ለሃገሩ የሚጫወተው ኦባምያንግ ቅዠት የሚመስለውን ወቅታዊ የክለብ አቋሙን በዚህ ውድድር ለመቀየር ተዘጋጅቷል። 

ከዲስፒሊን ግድፈት ጋር በተገናኘ አምበልነቱን የተቀማውና ከሚካኤል አርቴታ ቋሚ 11 ውጪ የተደረገው ኦባ በአርሰናል ቤት የተበላሸውን የእግር ኳስ ህይወቱን በካሜሩን ሊያድስ ይችላል? መልሱን ከውድድሩ ጅማሮ በኃላ ምንመለከተው ይሆናል። ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ፓትሪስ ኒቪው ትልቅ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚከብዳቸው ቢጠበቅም የቡድኑን አጠቃላይ ክብር መመለስ እና ጥሩ ውድድር ማሳለፍን ያልማሉ። 

ያለፈውን አፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ያልቻሉት ጋቦናውያን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችን በትልቅ ተስፋ ቢጀምሩም ተራራውን መሻገር ከብዶዋቸው ከግድግዳዎች ጋር የመላተም ጉዞ ሆኖባቸው አልፏል። እንደ ዲዲዬ ንዶንግ፣ ዬኒ ማትያስፖር የመሳሰሉ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾችን የደጋፊውን ድምፅ ሰምተው ያላካተቱት ኒቪው ይህን ያላደረጉት የቡድኑን መንፈስ ለመጠበቅ በማሰብ እንደሆነ ታምኖበታል። ከምድብ ማለፍ ከቻሉ ጥቋቁር ግስላዎቹ ውጤቱን በመልካም ያዩታል። 

ኮሞሮስ

ኮሞሮስ፡ እንደ ቤተሰብ የተገነባው ቡድን
  • ተሳትፎ፡  የመጀመሪያ ጊዜ 
  • ምርጥ ውጤት፡ –
  • አሰልጣኝ፡ አሚር አብዶ
  • ኮከብ ተጨዋች፡  ኤል ፋርዱ ቤን መሃመድ

ምን ይጠብቃሉ፡ የመድረኩ እንግዳዋ ሃገር ኮሞሮስ በቡድኗ ውስጥ ልምድን ያካበቱ ተጨዋቾች መያዟ በቀላሉ እንዳትታይ ያደርጋታል። ወረቀት ላይ ምንም ማድረግ እንደሚቻል ያምናሉ። ኦባምያንግን ከያዘችው ጋቦን ጋር በመክፈቻው ሲገናኙ ሽንፈትን ካስወገዱ ምንም ነገር ሊያደርጉ ይችላሉ። ለትንሿ የባህር ዳርቻ ሃገር ምንም ውጤት ቢመዘገብ ፋይዳው እምብዛም አለመሆኑ በጀብደኝነት እንዲጫወቱ ሊያደርጋቸው ይችላል።

የቡድኑ አምበል ናጂም አብዱ እና ጓደኞቹ ከግብፅ ጋር 0-0 የተለያዩበትን ውጤት ጨምሮ ከጋና፣ ካሜሩን እና ሞሮኮ ጋር ተገናኝተው ማወቃቸው በውድድሩ ላይ የራስ መተማመንን ይጨምርላቸዋል። ከምድብ ማለፍ ከቻሉ እንደ ትልቅ ውጤት ይቆጥሩታል። 

የጨዋታ መርሃ ግብሮች

ሰኞ ጥር 2/2014 

  • ሞሮኮ vs ጋና (ምሽት 1፡00 ሰዓት)
  • ኮሞሮስ vs ጋቦን (ምሽት 4፡00 ሰዓት)

አርብ ጥር 6/2014 

  • ሞሮኮ vs ኮሞሮስ (ምሽት 1፡00 ሰዓት)
  • ጋቦን vs ጋና (ምሽት 4:00 ሰዓት)

ማክሰኞ ጥር 10/2014

  • ጋቦን vs ሞሮኮ (ምሽት 4:00 ሰዓት)
  • ጋና vs ኮሞሮስ (ምሽት 4:00 ሰዓት) 

ምንጮች፡ 

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

 Three-time Olympic gold medalist Gabby Thomas has arrived in the Ethiopian capital ahead of the highly anticipated Addis Ababa Grand Prix. Her arrival marks a significant milestone for the region,…

Leave a Reply

You Missed

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

Saint George respond on the pitch 

Saint George respond on the pitch