ይስማው ድሉ እና መልክናት ውዱ የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ 10 ኪሎ ሜትር አሸነፉ

ይስማው ከሁለቱ አሸናፊዎች የበለጠ አሳማኝ የነበረ ሲሆን ፤ ውድድሩን በ28 ደቂቃ ከ25 ሰከንድ አጠናቋል። ይህም በ2006 ዓ.ም በድሪባ መርጋ ከተመዘገበው የውድድሩ ሪከርድ (28፡16) በ9 ሰከንድ ብቻ ዘግይቶ አጠናቋል። ይህ ድሉ ባለፈው ቅዳሜ በተካሄደው አገር አቋራጭ ማጣሪያ ላይ ለኢትዮጵያ ቡድን ማለፍ ባለመቻሉ የተሰማውን ቁጭት ያስረሳው ሲሆን ፤ በጎዳና እና በትራክ ላይ በሚያደርጋቸው ውድድሮች ግን ባለው ስኬት ላይ ተጨማሪ ድል ሆኖለታል።

ባለፈው ዓመት 3ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ይስማው ፤ በመስከረም ወር መጨረሻ በካርዲፍ ግማሽ ማራቶን በ59 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በማሸነፍ ጥሩ አቋም ላይ ሆኖ ነበር ወደዚህ ውድድር የመጣው። በበጋው መጨረሻ ላይ ደግሞ በ3፡58.7 በሆነ ሰዓት የመንገድ ማይል በመሮጥ በተለያዩ ርቀቶች ላይ ያለውን አቅም እያሳየ የሚገኝ ወጣት አትሌት ነው። በሁለተኛ ደረጃ አዲሱ ነጋሽ (28:28) እና በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ ድንቃለም አየለ (28:29) በመግባት አጠናቀዋል።

በሴቶች ከሁለት ዓመት በፊት የውድድሩ አሸናፊ የነበረችው መልክናት ውዱ ፤ በመጨረሻዎቹ 150 ሜትሮች ላይ ፍታው ዘርዓይን በማስቀደም ወደ ቀድሞ ፎርሟ መመለሷን አረጋግጣለች። ውዱ ከሁለት ሳምንት በፊት በቦስተን ግማሽ ማራቶን ከሀገሯ ልጅ ፋንታዬ በላይነሽ በመቀጠል 2ኛ ሆና ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ ይህም በበጋው ሁለተኛ አጋማሽ በደረሰባት ጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቃ ከቆየች በኋላ ነው።

ሁለቱም አሸናፊዎች እያንዳንዳቸው 400,000 የኢትዮጵያ ብር የገንዘብ ሽልማት አግኝተዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርት ህይወታቸው በሚቀጥሉበት ጊዜ የአሸናፊነት መለያው ለእነሱ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። ድሉ ቀጣይ ውድድሩን በታህሳስ 5 በሳውዲ አረቢያ የሚያደርግ ሲሆን፣ ወዱ ደግሞ ለሚቀጥለው የቤት ውስጥ ውድድር (Indoor season) ወደ ትራክ ለመመለስ ትፈልጋለች።ዛሬ መስመሩን ከተሻገሩ የመጀመሪያዎቹ አምባሳደሮች መካከል የኖርዌይ አምባሳደር ሲሆኑ፣ ውድድሩን በ49 ደቂቃ ከ3 ሰከንድ አጠናቀዋል።

ለታላቁ የኢትዮጵያ ሩጫ ተጋባዥ እንግዶች ሆነው የቀረቡት ዳንኤል ኮመን እና ኻሊድ ኻኑቺ ከብዙሃኑ ጋር ኮርሱን ያጠናቀቁ ሲሆን፣ በ44 ደቂቃ እና በ50 ደቂቃ በመግባት ውድድሩን አጠናቀዋል።

🥇 አሸናፊ ወንዶች

  1. ይስማው ድሉ 28:25.2
  2. አዲሱ ነጋሽ 28:28.6
  3. ድንቃለሙ አየለ28:29.2

🥇ሴቶች ሰዓት

  1. መልክናት ውዱ 32:11.2
  2. ፍታው ዘራይ 32:11.5
  3. መሰለች አለማየሁ 32:19.7

Via Great Ethiopian Run

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    Diribe Welteji banned for two years

    The Court of Arbitration for Sport (CAS) has partially upheld an appeal by World Athletics against the Ethiopian National Anti-Doping Office (ETH-NADO) and middle-distance runner Diribe Welteji Kejelcha (Ethiopia). Ms…

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    የቀድሞው የቼልሲ የመሀል ተከላካይ ጆን ቴሪ ጥር ላይ በተሰናበቱት አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ ምትክ የጊዜያዊ አሰልጣኝነት እድል ባለማግኘቱ ደስተኛ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡  ጆን ቴሪ በቼልሲ አካዳሚ በበጎ ፈቃድ አሰልጣኝነት በወር ሁለት ቀን…

    You Missed

    Ethiopia Bunna appoints new chairman 

    Ethiopia Bunna appoints new chairman 

    Diribe Welteji banned for two years

    Diribe Welteji banned for two years

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    ጆን ቴሪ በቼልሲ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት ምርጫ ማዘኑን ገልጿል

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

    ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

    ከራባት እስከ አጋዲር፡ AFCON 2025ን የሚያስተናግዱ ዘጠኝ ስታዲየሞች

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ

    የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዳሰሳ