ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ህዳር 14 ቀን በሚደረገው የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ላይ ለሚያሸንፉ አትሌቶች በድምሩ ከ1.8ሚሊዮን ብር በላይ ሊሸልም ነው።

ከ2017 ዓ.ም. ጀምሮ የአለም አትሌቲክስ (Label Road Race) ደረጃ የተሰጠው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ሃያ አምስተኛ ዓመት ውድድሩን በማስመልከት በአንደኛነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሚያበረክተውን የገንዘብ ሽልማት ወደ አራት መቶ ሺህ (400,000) ብር ከፍ አድርጓል።

በዚህም መሰረት ሽልማቱ በውድድሩ ላይ ባለፈው አመት ለአሸናፊዎች በሽልማትነት ተበርክቶ ከነበረው 250ሺህ ብር በስልሳ በመቶ (60%) አድጓል። በተመሳሳይ ሁለተኛ ለሚሆኑ የ200ሺህ አንዲሁም ሶስተኛ ሆነው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የ100ሺህ ብር ሽልማት አንደሚበረከት ይፋ ተደርጓል።

የውድድሩን ጥራት አና የአትሌቶችን ፉክክር ከፍ ማድረግ አንዲቻልም በክለብ አና የስፖርት ማኔጅመንት ውስጥ ከሚገኙ አትሌቶች በተጨማሪ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች ዕድል ለመፍጠር ቅዳሜ ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም. በእንጦጦ ፓርክ የማጣሪያ ውድድር ይካሔዳል። ይህም ማጣሪያ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች በውድድሩ ላይ የመሳተፍ ዕድልን ይፈጥርላቸዋል።

ቅዳሜ ከአትሌቶች የማጣሪያ ውድድር በተጨማሪም 9ኛው ዙር የወርሃዊው እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ ባለፉት ውድድሮች ላይ ሰባት እና ከዛ በላይ ለሆነ ጊዜ የሮጡ ተሳታፊዎች ልዩ ሽልማት ይበረከትላቸዋል።

(ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ)

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

Gudaf Tsegay banned for four months

Decorated two-time former World champion and Olympic medallist, Gudaf Tsegay, has been banned for four months by the Athletics Integrity Unit (AIU) under a Case Resolution Agreement, after admitting to…

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

The Ethiopia national under-17 football team will face Mozambique national under-17 football team in a play-off match that will determine qualification for the FIFA U-17 World Cup. Ethiopia defeated Tunisia…

You Missed

Gudaf Tsegay banned for four months

Gudaf Tsegay banned for four months

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች