ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለአትሌቶች ከፍተኛውን ሽልማት ሊያበረክት ነው

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ህዳር 14 ቀን በሚደረገው የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ላይ ለሚያሸንፉ አትሌቶች በድምሩ ከ1.8ሚሊዮን ብር በላይ ሊሸልም ነው።

ከ2017 ዓ.ም. ጀምሮ የአለም አትሌቲክስ (Label Road Race) ደረጃ የተሰጠው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ሃያ አምስተኛ ዓመት ውድድሩን በማስመልከት በአንደኛነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሚያበረክተውን የገንዘብ ሽልማት ወደ አራት መቶ ሺህ (400,000) ብር ከፍ አድርጓል።

በዚህም መሰረት ሽልማቱ በውድድሩ ላይ ባለፈው አመት ለአሸናፊዎች በሽልማትነት ተበርክቶ ከነበረው 250ሺህ ብር በስልሳ በመቶ (60%) አድጓል። በተመሳሳይ ሁለተኛ ለሚሆኑ የ200ሺህ አንዲሁም ሶስተኛ ሆነው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የ100ሺህ ብር ሽልማት አንደሚበረከት ይፋ ተደርጓል።

የውድድሩን ጥራት አና የአትሌቶችን ፉክክር ከፍ ማድረግ አንዲቻልም በክለብ አና የስፖርት ማኔጅመንት ውስጥ ከሚገኙ አትሌቶች በተጨማሪ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች ዕድል ለመፍጠር ቅዳሜ ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም. በእንጦጦ ፓርክ የማጣሪያ ውድድር ይካሔዳል። ይህም ማጣሪያ በግል ለሚወዳደሩ አትሌቶች በውድድሩ ላይ የመሳተፍ ዕድልን ይፈጥርላቸዋል።

ቅዳሜ ከአትሌቶች የማጣሪያ ውድድር በተጨማሪም 9ኛው ዙር የወርሃዊው እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ ባለፉት ውድድሮች ላይ ሰባት እና ከዛ በላይ ለሆነ ጊዜ የሮጡ ተሳታፊዎች ልዩ ሽልማት ይበረከትላቸዋል።

(ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ)

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

via Great African Run ዋሽንግተን ዲሲ:- ዝነኛው የኬንያ የረጅም ርቀት ሯጭ ፖል ቴርጋት ኦክቶበር 10 ቀን 2026 በአሌክሳንድሪያ፣ ቨርጂኒያ በሚካሄደው ግራንድ አፍሪካን ረን የክብር እንግዳ ሆኖ እንደሚሳተፍ አዘጋጆቹ አስታወቁ። ፖል…

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Addisu Gobena wins Sydney Marathon with course-record performance Ethiopian athlete Addisu Gobena won the Sydney Marathon on Saturday August 30, setting a new course record at the World Athletics Platinum Label event.…

You Missed

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Abubeker Nassir has joined Mechal

Abubeker Nassir has joined Mechal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።