25ኛ ዓመት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ህዳር 14 / 2018 ዓ.ም. ይካሔዳል

  • News
  • April 25, 2025
  • 0 Comments

የብር ኢዮቤልዩ ላይ የደረሰው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ሊከናወን ሰባት ወራት ቀሩት። ህዳር 16 ቀን 1994ዓ.ም. ጅማሮውን ያደረገው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በቀጣይ ህዳር 14 ቀን 2018ዓ.ም. 25ኛ ዙር ውድድሩን ያከናውናል።

ከአፍሪካ ትልቁ የ10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ውድድር የሆነው ዝግጅቱ ባለፉት 24 የውድድር ዓመታት ወደ 760ሺህ አካባቢ ሰው በ10ኪ.ሜ. ውድድሩ ላይ አሳትፏል።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የዘንድሮ ውድድር በተጠናቀቀ ማግስት የ25ኛ ዓመት ክብረበዓሉን አስመልክቶ ለቀጣዩ ዓመት 500 ቀዳሚ ተሳታፊዎች በነጻ ምዝገባ ያከናወነ መሆኑ ይታወሳል። ለሌሎች የውድድሩ ተሳታፊዎች ምዝገባ ሐምሌ ወር ላይ እንደሚከናወን ተገልጿል።

“25ኛ ዓመታችንን አብረውን በመሆን ካበረቱን ሁሉ ጋር ለማክበር ተዘጋጅተናል ፤ ደስታችንን ከራሳችን ለመጀመር በዚህ እሁድ ኬንያ በሚደረገው ኤልዶሬት ማራቶን ላይ ተሳትፈን እና ሩጫችንን አስተዋውቀን እንመለሳለን።” ያሉት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ “ከወዲሁ ከሩጫችን ጋር የተያያዙ የተሳታፊዎቻችንን ልዩ ልዩ ታሪኮች እና ገጠመኞች መሰብሰብ ስለጀመርን በማህበራዊ ሚድያ ገጾቻችን ላይ ቢነገር የሚሉትን ትውስታቸውን ያካፍሉን” ሲሉ ለተሳታፊዎች ጥሪ አቅርበዋል።

ከ24 ዓመታት በፊት ውድድሩ ሲጀመር ኃይሌ ገብረስላሴ እና ብርሃኔ አደሬ የመጀመሪያውን ዓመት ውድድር ያሸነፉ አትሌቶች ሲሆኑ ፤ በዘንድሮ ውድድር ላይ ወጣቶቹ አትሌቶች ቢንያም መሃሪ እና አሳየች አይቸው ማሸነፋቸው ይታወሳል።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተሳታፊዎች ትዝታዎቻቸውን በ communications@ethiopianrun.org ላይ ማጋራት እንደሚችሉ ገልጿል።

  • Girmachew Kebede

    Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

    Related Posts

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

     Three-time Olympic gold medalist Gabby Thomas has arrived in the Ethiopian capital ahead of the highly anticipated Addis Ababa Grand Prix. Her arrival marks a significant milestone for the region,…

    You Missed

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    Saint George respond on the pitch 

    Saint George respond on the pitch