ፌዴሬሽኑ እና የሊግ ተሳታፊዎችን ቁጥር ማሳደግ

  • amharic
  • August 12, 2025
  • 0 Comments

ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ሲዳማ ቡና የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት /ካስ/ የፅሁፍ ምልልስ የተረዳሁት ነገር ፌዴሬሽኑ የፕሪምየር ሊግ ክለቦችን 20 ለማድረግ ያቀረበው ምክንያት ምንም አይነት ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን ነው::

እንደምታስታውሱት ፌዴሬሽኑ ሊጉን ወደ 20 ክለቦች ለማሳደግ ያቀረበው ምክንያት በፕሪምየር ሊጉ የፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከተመረመሩት እና በኋላም ከተቀጡት አራት ክለቦች ውጭ ያሉት ክለቦች አለመመርመራቸውን እና በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ መሰረት ከጥፋት ነፃ መሆናቸው አለመረጋገጡ ነው::

ምስል 1- የፌደሬሽን ምክንያት

ሲዳማ ቡና ለ”ካስ” ባስገባው መከራከሪያ ሌሎቹ ክለቦች አለመመርመራቸውን በምክንያት በማቅረብ ምርመራው በዘፈቀደ የተደረገ መሆኑን ይገልፃል:: በዚህም አራቱ ክለቦች ተለይተው መቀጣታቸው አድሏዊ እና ኢፍትሀዊ [የውድድር] ከባቢ በመፍጠር ሲዳማ ቡና እና ሌሎቹ ሶስት ክለቦች ተገቢ ያልሆነ ኢላማ እንዲሆኑ ተደርገዋል ይላል:: (ምርመራውን ያደረገው ፌዴሬሽኑ እንዳልሆነ ልብ ይሏል)


ፌዴሬሽኑ በምላሹ በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ መሰረት የፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴው ክለቦችን በዘፈቀደ መርጦ የመመርመር መብት እንዳለው ገልፇል:: ስለዚህ ሲዳማ ቡና እና ሌሎች ሶስት ክለቦች ተለይተው መመርመራቸው እና መቀጣታቸው የህግ ጥሰት እንደሌለበት በፅሁፍ ተከራክሯል::


የእኔ ጥያቄ እዚህ ላይ ነው:: በፌዴሬሽኑ የህግ ምላሽ መሰረት የ14ቱ ክለቦች አለመመርመር ምንም አይነት የህግ ጥሰት ከሌለበት “ገና ለገና አጥፍተው ይሆናል: ነፃ አይሆኑም” በሚል የሊጉን ተሳታፊዎች ቁጥር ማሳደግ የህግ መሰረቱ ምንድን ነው? ክለቦቹ በእግር ኳሱ የፍትህ አካላት ጥፋተኛ እስኪባሉ ድረስ ነፃ መሆናቸውንስ አይቃረንም? ፌዴሬሽኑ ለ”ካስ” የህግ ጥሰት የለም እያለ በሀገር ውስጥ ውሳኔዎቹ ግን ስህተት እንዳለ የሚያሳይ ውሳኔ መወሰኑ አይቃረንም?

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዛሬ የ2019 ዓ.ም. ዓለም አቀፍ 10 ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባን በይፋ አስጀምሯል። ውድድሩ እሑድ ህዳር 13 ቀን 2019 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን፣ በዚህ ዓመት በታሪኩ ከፍተኛውን 60,000…

የጀርመን ስንብት ሲቃኝ

የጀርመን ብሄራዊ ቡድን ከ2026ቱ የአለም ዋንጫ በፓራጏይ 4-3 በፍፁም ቅጣት ምት ተረቶ ተሰናብቷል::  በዚህም መሀል አሰልጣኝ ጁሊያን ናግልስማን ከባድ ትችት እየገጠመው ነው::  የቀድሞው የጀርመን እና አርሰናል ግብ ጠባቂ የንስ ሌማን…

You Missed

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Abubeker Nassir has joined Mechal

Abubeker Nassir has joined Mechal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።