አቋማቸው የዋዠቀ አምስት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች

ሁለቱ የማንችስተር ክለቦችን ጨምሮ 5 ቡድኖች ባለፉት ሶስት አመታት የዋዥቀ አቋምን እንዳሳዩ CryptoCasinos  ያወጣው ቁጥራዊ መረጃ ያሳያል::

  1. ማንችስተር ዩናይትድ

የ20 ጊዜ የፕሪሚየር ሊግ አሸናፊዎቹ ከትልቁ ዋንጫ ከራቁ 12 አመታት ተቆጥረዋል:: ከ2022/23 አንፃር ዩናይትድ 33 ነጥቦች ሲቀንሱ 12 ጨዋታዎችን ሳያሸንፉ ቀርተዋል:: ከዚህም በተጨማሪ ያስቆጠሯቸው ግቦች በ14 አንሰዋል::

2. ቶተንሀም ሆትስፐር

ቶተንሀም በበኩላቸው በ3 የውድድር ዘመናት 22 ነጥቦች ቀንሰዋል:: በእነዚህም ጊዜያት 48 ጨዋታዎችን ተሸንፈዋል::

3. ማንችስተር ሲቲ

ለአራት ተከታታይ አመታት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ማሸነፍ የቻሉት ማንችስተር ሲቲ ሳይቀሩ ባለፉት ሶስት አመታት የአቋም መዋዥቅ አሳይተዋል፡፡ ሲቲ በሶስቱ የውድድር አመታት 251 ነጥቦችን ሰብሰባዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ 77 ጨዋታዎችን አሸንፈዋል፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን በ18 ነጥቦች እና 7 ድሎች አንሰው ተገኝተዋል፡፡

4. አርሰናል

ለተከታታይ ሶስት አመታት ሶስተኛ በመሆን ያጠናቀቁት አርሰናል ከአመት አመት ነጥቦቻቸው እየቀነሱ ነው፡፡ በአጠቃላይ 247 ነጥቦች እና 15 ሽንፈቶች ቢያጋጥማችማውም በእነዚህ አመታት በ10 ነጥብ መቀነሳቸው ዋንጫውን እንዳያነሱ ምክንያት ሆኖባቸዋል፡፡

5. ኒውካስል ዩናይትድ

ከዝርዝር ውስጥ ካሉት ከለቦች ኒውካስል ዩናይትድ የተሻለ እንቅስቃሴ አላቸው፡፡ የቀነሱት ነጥብም 5 ብቻ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

ከተጀመረ ሶስተኛ ሳምንት ላይ በደረሰው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሊቨርፑል በክረምቱ ካደረጉት መጠናከር በኋላ ጠንካራ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ “የአለም አትሌቲክስ ማራቶን ሻምፒዮና” በማዘጋጀት ለወደፊቱ የረጅም ርቀት ሩጫ ትልቅ ነገርን አሰናድቷል። ማራቶን በ2027 እና 2029 የአለም አትሌቲክስ ውድድሮች ላይ እንደ አንዱ የውድድር አይነት ሆኖ የሚቀጥል…

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አሰልጣኝ አግኝቷል

    የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌን ቀጣዩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ በመምረጥ ውሳኔ አሳልፏል። አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌ በአሁኑ ወቅት የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ሆነው…

    You Missed

    ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

    ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

    Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

    Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

    Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

    Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

    Abubeker Nassir has joined Mechal

    Abubeker Nassir has joined Mechal

    Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

    Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

    የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

    የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።