ከጥቂት አመታት በፊት ይህ ነው የሚባል የዘጠኝ ቁጥር ተጫዋች አልነበረም፡፡ ይህም በርካታ ታላላቅ የአውሮፓ ክለቦችን ያሳስብ ነበር፡፡ በተለይም በ2010ቹ ገነው ከወጡት እንደሉዊስ ስዋሬዝ ፤ ሰርጂዮ አግዌሮ ፤ ካሪም ቤንዚማ ፤ ሮበርት ሌቫንዶቭኪ እና ኤዲንሰን ካቫኒ በሃላ ልዩ ችሎታ ያለው እና ማራኪ አጥቂ ለማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል፡፡ በርካታ ክለቦችም አይናቸውን እንግሊዛዊው ሀሪ ኬን ላይ አድርገው ነበር፡፡ እርሱ ግን ከተጠበቀው በላይ ቆይታውን በቶተንሀም አድርጓል፡፡ ማንችስተር ሲቲ እርሱን ለማስፈረም ያልፈነቀለውን ድንጋይ ልብ ይሏል፡፡
በእነዚህ ጊዜያቶች ውስጥ አርሰናል ፒየር ኤመሪክ አውባሜያንግ እና አሌክሳንደር ላካዜትን አስፈርሟል፡፡ ማን ሲቲ ያለ አጥቂ የተጫወቱበት የውድድር ዘመን ነበር ( 2021/22)፡፡ ቼልሲ አልቫሮ ሞራታን ሲሞክሩ ማንችስተር ዩናይትድ ለሮሜሉ ሉካኩ እድልን ሰጥተዋል፡፡
በአሁኑ የክረምት የዝውውር መስኮት ነገሮች የተቀያየሩ ይመስላሉ፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ ቤንጃሚን ሼሽኮን ከላይፕዚሽ አስፈርሟል፡፡ ቼልሲ ጆዋአ ፔድሮ እና ሊያም ዴላፕን አክሏል፡፡ ሊቨርፑል ሁጎ ኢኪቲኬን እና አርሰናል ደግሞ ቪክቶር ዮኮሬስን የግላቸው አድርገዋል፡፡
የሊቨርፑል ቢዝነስ ግን አላለቀም፡፡ የኒውካስል ዩናይትዱን አሌክሳንደር ኢሳክ ይፈልጋሉ፡፡ ኒውካስል በበኩላቸው ስትራድ ላርሰንን ከዎልቭስ ዋልተማደን ከሽቱትጋርት ለማምጣት እየተጉ ነው፡፡ የዊሳም ጉዳይ ገና አላበቃም፡፡
ይህ ሁሉ አጥቂ ከየት መጣ?
እግር ኳስ ተለዋዋጭ ስፖርት መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በተለይም አሁን ባለንበት ዘመን ከፍተኛ የሆነ የታክቲክ እና ቴክኒክ ለውጦች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ቀጣዩ ትልቅ revolution አጥቂዎች ላይ የሚያተኩር ይመስላል፡፡
እንደኢኪቲኬ፤ አይዛክ፤ ዋልተማደ እና ጉራሲ አይነት ረጅም ሆነው ከእግር ኳስ ጋር ምቾት የሚሰማቸው ተጫዋቾች ተመራጭ ሆነዋል፡፡ እነዚህ ተጫዋቾች ግብ ማስቆጠር የሚችሉት ከርቀት ወይንም በቅርበት በእግራቸው tap in ብቻ ሳይሆን በግንባራቸውም ጭምር ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ኳስ ምስረታ ላይ የላቀ ሚና አላቸው፡፡ hold play ላይ የላቁ ናቸው፡፡ ይታትራሉ፡፡ ብቻ ምን አለፋችሁ the full package ናቸው፡፡






