ሌስተር ሲቲ ከ አርሴናል: የትሮሳርድ ልዩ ሚና እና የሌስተር ሲቲ ምላሽ

አርሴናል ወደ ኪንግ ፓወር ስቴድየም ተጉዞ ሌስተር ሲቲን በማሸነፍ በዋንጫው ፉክክር መሪነቱን ያስቀጠለበት ሦስት ነጥብ ማግኘት ችሏል።

ሁለተኛው አጋማሽ ጅማሬ ላይ በማርቲኔሊ  ብቸኛ ጎል ጨዋታውን ማሸነፍ የቻሉት መድፈኞቹ በጨዋታው ከወትሮው ለየት ያለ አቀራረብ ይዘው ቀርበዋል። ይህም በፊት መስመር አጥቂነት ትሮሳርድ መሰለፉ ነው። በእንቅስቃሴም ተጨዋቹ ሃሰተኛ ዘጠኝ ቁጥር ሚናን ሲተገብር ተስተውሏል።

ሃሰተኛ ዘጠኝ ቁጥር ሚና እግርኳስ ቅርፅ እና ወግ ይዞ መካሄድ ከጀመረ ወዲህ በርካቶች የተለያየ ጊዜ ላይ መተግበር እንደተጀመረ ያስረዳሉ። ያም ሆነ ይህ ሃሰተኛ ዘጠኝ ቁጥር ሚናን ሊዮኔል ሜሲን በመጠቀም የፔፕ ግዋርድዮላን ያህል የተገበረ አለመኖሩ ያስማማል።

ሃሰተኛ ዘጠኝ ቁጥር ሚና ትርጉሙ እንደወረደ፤ አጥቂ(9 ቁጥር) ተጨዋች ሊገኝ ከሚገባው ቦታ ውጪ አብዛኛውን የጨዋታ ጊዜ ሲያሳልፍ ነው። ይህም በተጠና አካሄድ የተጋጣሚን ተከላካይ(የ9 ቁጥሩን ማርከር) ቦታውን አስለቅቆ በሌሎች ተጨዋቾች ይተለቀቅውን ‘ስፔስ’ ማጥቃት ነው።

ሌስተር ሲቲዎች ለአርሴናል ለወጥ ያለ አቀራረብ የሰጡት ምላሽ ትኩረትን የሚስብ ነበር። የጨዋታውን አብዛኛው ክፍለጊዜም በፋያስ የሚመራው የተከላካይ ክፍል የትሮሳርድን እንቅስቃሴ መቆጣጠር ችሏል።

እንዴት?

የሌስተር ሲቲ መኅል ተከላካይ እና መሪ ፋዬስ በትሮሳርድ ከመሳብ ይልቅ የኋላ 4 ተጨዋቾችን(እራሱን ጨምሮ) መስመር ጠብቆ ይገኝ ነበር። ትሮሳርድን በሳጥን ውስጥ የፋዬስ ሃላፊነት ሲሆን ተጨዋቹ በጥልቀት ሲመለስ ደግሞ የተከላካይ አማካዩ ንዲዲ ሃላፊነቱን ይረከባል።

በምስሉ ላይ እንደሚታየው፣ ትሮሳርድ በጥልቀት ተመልሶ ኳስ ሲቀበል ንዲዲ ይጫነዋል።

የተለቀቀ ክፍተት ባለመኖሩ የአርሴናል መስመር አትቂዎች ሩጫዎችን ማድረግ አይችሉም። ትሮሳርድ ያለው አማራጭ ኳሱን ወደ መስመር ለሳካ ማውጣት ነው።

ሳካ በነፃነት መስመር ላይ ኳስ ቢያገኝም ከክሮስ ውጪ አማራጭ ያለው አይመስልም::

ወደ መስመር የወጣውን ኳስ ከሳካ ተቀብሎ ኋይት ቢያሻግርም፣ በቁጥር ሳጥን ውስጥ የነበሩት የሌስተር ሲቲ ተከላካዮች ትሮሳርድን ጨምሮ ኳሱን ለመግጨት የተገኙትን የአርሴናል ተጨዋቾች እድል አልሰጡም።

በሌላ አጋጣሚም በትሮሳርድ እንቅስቃሴ የተሳበው ፋዬስ በእጅ ምልክት ከንዲዲ ጋር ሲነጋገር ይታያል።’የአንተ ሃላፊነት ነው የሚል ምልክት’

ወድያውም ንዲዲ ወደ ትሮሳርድ፣ ፋዬስም ወደ ኋላ መስመሩ…

የመጀመርያውን አጋማሽ ከሞላ ጎደል የአርሴናልን የማጥቂያ ቀጠና እንቅስቃሴ መገደብ የቻሉት ሌስተሮች በሁለተኛው አጋማሽ መጀመርያ ደቂቃዎች ባሳዩት መዘናጋት ዋጋ ከፍለዋል።

ከግብ ጠባቂ መስርተው ለመውጣት በሚሞክሩበት ሰዓት የቀኝ ተከላካዩ ካስታኜ ሁለተኛው የሜዳ ክፍል ላይ ይገኛል።

ካስታኜ በሁለተኛው የሜዳ ክፍል ኳስን ተቀብሎ ለመጫወት ቢሞክርም የአርሴናል ካውንተር ፕሬስ ፋታ የሚሰጥ አልነበረም። ጋብሬል ማጋሌሽ ለማፅዳት የሞከረውም ኳስ በዕድል በሚመስል መልኩ የካስታኜን የተከፈተ ቀጠና ላይ የነበረው ትሮሳርድ አገኘ።

የአርሴናል የማጥቃት ሽግግር ከመጀመርያው አጋማሽ በተቃራኒ ቅርፁን ላጣው የሌስተር ኋላ መስመር ለመቋቋም ከባድ ነበር። ማርቲኔሊ ጎሉን ለማስቆጠር ያደረገው የሽምጠጣ ሩጫ እና የተረጋጋ አጨራረስ አስገራሚ ነበር።

ከዚህ ጨዋታ ሌስተር ሲቲ ምንም ናገር ይዘው መውጣት ባይችሉም፣ ብጨዋታውም የማጥቃት እንቅስቃሴያቸው እምብዛም ባይሆን፤ ለአርሴናል የሃሰተኛ ዘጠኝ ቁጥር የአጨዋወት ስልት አስተማሪ የሆነ ምላሽን ሰጥተዋል።

  • Minyahel Mamo

    Related Posts

    በታላላቆቹ የአውሮፓ ሊጎች ግቦችን እያመረቱ ያሉ አምስት ተጫዋቾች

    በዘንድሮው የውድድር ዘመን በአምስቱ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ከዚህ በፊት በግብ አስቆጣሪነታቸው የሚታወቁት ተጫዋቾች አሁንም ግብ ማምረታቸውን ቀጥለውበታል፡፡ እንደሀሪ ኬን ፤ አርሊንግ ሀላንድ እና ኪሊያን ምባፔ ያሉ ተጫዋቾች በርካታ ግቦችን በማስቆጠር…

    አዲሱ የአሎንሶ አብዮት; የጨዋታ ቁጥጥር እና ከኳስ ውጪ የተጨዋቾች ሚና

    ከላይ የተጠቀሱት ሃሳቦች አውሮፓ ውስጥ ላሉ ታላላቅ ክለቦች እና አሰልጣኞቻቸው አዲስ ነገር አይደሉም:: በእግርኳስ ከፍ ባለው ልህቀት ደረጃ ላይ የደረሱ አሰልጣኞች ዋነኛ አላማቸው የጨዋታውን አካሄድ መቆጣጠር ነው:: ይህም ተጋጣሚን አጨዋወቱን…

    Leave a Reply

    You Missed

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    Saint George respond on the pitch 

    Saint George respond on the pitch