የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዛሬ የ2019 ዓ.ም. ዓለም አቀፍ 10 ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባን በይፋ አስጀምሯል። ውድድሩ እሑድ ህዳር 13 ቀን 2019 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን፣ በዚህ ዓመት በታሪኩ ከፍተኛውን 60,000 ተሳታፊዎች ለመቀበል ዝግጅት ተደርጓል።

ይህ ውድድር በተጨማሪም ባንክ ኦፍ አሜሪካ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና አጋር (Presenting Partner) ሆኖ የሚጀምርበት የውድድር ዓመት ይሆናል።

ባለፈው ህዳር ወር የተፈረመውን ስምምነት ተከትሎ፣ በአፍሪካ ትልቁ የጎዳና ላይ ሩጫ በ2030 ዓ.ም. የዓለም ትልቁ 10 ኪ.ሜ. ሩጫ ለመሆን ያለመ ሲሆን፣ ለበርካታ ወጣቶች የመሳተፍ እድልን በማስፋትና በህጻናት ውድድሮች ተሳትፎን በማሳደግ ይህን ግብ ለማሳካት እየሰራ ይገኛል።

የ10 ኪ.ሜ. ውድድሩ ተሳታፊዎች ቁጥር ከፍ እያለ ከመምጣቱ ባሻገር በአንድ ቀን ልዩነት የሚካሔደው የህጻናት ሩጫም በተሳታፊ ቁጥር በማደግ 5,000 ህጻናት እንዲሳተፉበት ይደረጋል።

በተጨማሪም፣ ባንክ ኦፍ አሜሪካ በየዓመቱ በዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዙሪያ በሚካሄደው የ’ቅድሚያ ለሴቶች የ5ኪ.ሜ. ሩጫ’ (Women First 5km) ውድድርም ዋና አጋር ሆኗል።

የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዳግማዊት አማረ ዛሬ በተካሄደው የምዝገባ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት እንደተናገሩት “ዛሬ በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጉዞ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የምንከፍትበት ቀን ነው። ዓላማችን የዋና ውድድራችንን ተፅዕኖ በወጣቶች ዕድል ፈጠራ፣ በስፖርት ቱሪዝም እና በአካባቢያዊ ኢኮኖሚ ላይ ይበልጥ ማሳደግ ነው። ከባንክ ኦፍ አሜሪካ ጋር የጀመርነው አዲስ አጋርነት እንዲሁም ከሌሎች አጋሮቻችን የምናገኘው ቀጣይ ድጋፍ ለወደፊቱ ብዙ አዳዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥር በታላቅ ተስፋ እንጠብቃለን” ሲሉ በተጨማሪም ውድድሩ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ የዓለም ትልቁ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ለመሆን ያለውን ራዕይ ገልጸዋል።

ከሰሃራ በታች ባሉ ሃገራት የባንክ ኦፍ አሜሪካ የበላይ ኃላፊ የሆኑት ይቮን ኢኬ በላኩት መልዕክት “ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ማህበረሰቦችን ለማቀራረብ፣ ቀጣዩን ትውልድ ለማነሳሳት እና ኢትዮጵያን ለአለም ለማስተዋወቅ አቅም ያለው መድረክ ሆኗል። ተፅዕኖው ከዕለት ውድድርነት ባለፈ የኢኮኖሚ ዕድሎችን የሚፈጥር እና የአካባቢ ንግድ ድርጅቶችን የሚደግፍ ነው ፤ እኛም ከእንደዚህ አይነት ዝግጅት ጋር አጋር በመሆናችን ኩራት ይሰማናል። በአንድነት ሆነን ተሳትፎውን ለማስፋት፣ ተጨማሪ ወጣቶችንና ሴቶች እንዲሳተፉ ለማበረታታት እና ከአፍሪካ በጣም ታዋቂ የስፖርት ዝግጅቶች አንዱ የሆነበትን የስፖርት ግፅታ ለማጠናከር እንሰራለን” ብለዋል።

ውድድሩ ከ2017ዓ.ም. ጀምሮ የወርልድ አትሌቲክስ ሌብል ዕውቅና ያገኘ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖው እያደገ የመጣ ሲሆን፤ አብዛኛው ተሳታፊ ኢትዮጵያዊ ቢሆንም አለም አቀፍ ሯጮችም የውድድሩ አካል ይሆናሉ።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በህዝባዊነቱ እና በተሳታፊዎቹ ውበት እንዲሁም በኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ በሚፈጥረው የኩራትና የአንድነት ስሜት የሚታወቅ ውድድር ነው። በዚህ መሰረት፣ በተሳታፊዎች የዕድሜ ስብጥር ውስጥ ያለውን ክፍተት ለመሙላት፣ ከጠቅላላው የምዝገባ ቁጥር 5 በመቶ የሚሆነውን (3,000 የመሮጫ ቦታ) በነፃ በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍልን ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ተመድቧል።

በተጨማሪም፣ በውድድሩ የ26 ዓመት ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንድ ሰዓት በታች እንሮጣለን በሚል በአረንጓዴው መነሻ ላይ ለሚመዘገቡ ተሳታፊዎች የሰአት መቆጣጠርያ ቴክኖሎጂ ሥራ ላይ ይውላል። እንዲሁም ሁሉም ተሳታፊዎች ለውድድሩ በተሻለ ሁኔታ እንዲዘጋጁና ሩጫን የዕለት ተዕለት የአኗኗር አካል እንዲያደርጉ፣ በአዲሱ የልምምድ መተግበሪያ (Training App) እንዲመዘገቡና እንዲጠቀሙ ይበረታታል።

በተጨማሪም በዛሬው የምዝገባ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ፣ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ለሚያካሒደው ‘ሌሎችን ለመርዳት እሮጣለው’ [Run For A Cause] የድጋፍ ማሰባሰቢያ ዘመቻ በኦንላይን GivenGain ድረ-ገፅ አማካኝነት የሚሰበሰበውን ድጋፍ የበለጠ ለማሳደግ ያዘጋጀውን ዕቅድ ይፋ አድርጓል። በዚህ ዓመት ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰባሰብ ግብ የተቀመጠለት ይህ ዘመቻ፣ በኢትዮጵያ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተመረጡ ሶስት ተቋማትን ተጠቃሚ ያደርጋል።

በ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ግለሰቦች ምዝገባቸውን በቴሌብር መተግበሪያ ብቻ ማከናወን ይችላሉ። የምዝገባ ዋጋው ከመስቀል አደባባይ ለሚጀምረው ቀይ መነሻ 790 ብር፣ ከግዮን ሆቴል ፊት ለፊት ለሚጀምረው እና የሰአት መቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂ ለሚኖረው አረንጓዴ መነሻ 950 ብር መሆኑ ተገልጿል።

የዘንድሮው የውድድሩ መሪ ቃል (Race theme) “ሩጫዬ ቀለሜ” (My Run, My Color) ሲሆን፣ የውድድሩ ዋና የስያሜ አጋር (Presenting Partner) ባንክ ኦፍ አሜሪካ ነው። በተጨማሪም ዩኒሴፍ (UNICEF)፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ቴሌ ብር፣ ሶፊ ማልት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ሶሲ ሶያ፣ ፋብ ሳሙና፣ ህያት ሪጀንሲ አዲስ አበባ፣ ቶፕ ውሃ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC)፣ እንዲሁም አፍራን ሆስፒታል ለውድድሩ ስኬት በአጋርነት የሚሰሩ ተቋማት ናቸው።

Source- Great Ethiopian Run

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

Senaf Wakuma joins Simba Queens in Tanzania

Ethiopian striker Senaf Wakuma has made the move to Tanzanian outfit Simba Queens on a one-year contract.  Senaf has had a successful time in the Ethiopian Women’s Premier League, where…

የጀርመን ስንብት ሲቃኝ

የጀርመን ብሄራዊ ቡድን ከ2026ቱ የአለም ዋንጫ በፓራጏይ 4-3 በፍፁም ቅጣት ምት ተረቶ ተሰናብቷል::  በዚህም መሀል አሰልጣኝ ጁሊያን ናግልስማን ከባድ ትችት እየገጠመው ነው::  የቀድሞው የጀርመን እና አርሰናል ግብ ጠባቂ የንስ ሌማን…

You Missed

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

Senaf Wakuma joins Simba Queens in Tanzania

Senaf Wakuma joins Simba Queens in Tanzania

የጀርመን ስንብት ሲቃኝ

የጀርመን ስንብት ሲቃኝ

Gudaf Tsegay banned for four months

Gudaf Tsegay banned for four months

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw