የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆኑ

የ2025 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር ተሸላሚዎች ታውቀዋል። ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ስነ ስርአት በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የሚሰናዳ ነው። በየአመቱ ከስፖርት፣ ከስነ ጥበብና ከቢዝነስ ዘርፎች ለማህበረሰቦቻቸው ላበረከቱት አስተዋፅኦና ለለውጥ ላደረጉት የላቀ ተሳትፎ ከየዘርፉ ተመርጠው የሚሸለሙበት መድረክ ነው።

አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለ5 ጊዜያት ተካሂዷል። እውቅና ከተሰጣቸው ተፅዕኖ ፈጣሪዎች መካከል ደግሞ የሚከተሉት ይገኙበታል፦

2019: ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን( ቴዲ አፍሮ)፣ አትሌት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉና ሚስተር ማርክ ጌልፋንድ

2020: በኮቪድ-19 ምክንያት አልተካሄደም

2021: አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ፣ ድምፃዊ ኤኮንና አቶ በረከት ወልዱ

2022: አትሌት ቀነኒሳ በቀለ፣ “እረኛዬ” የቴሌቪዥን ድራማ፣ አቶ ሄኖክ ተስፋዬ እና ንግስት ሰናይ ልኬ

2023: የዲባባ ቤተሰብ፣ አቶ ግርማ ዋቄ፣ አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄና አትሌት ስለሺ ስህን

2024: ድምፃዊት አስቴር አወቀ፣ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ አትሌት ትዕግስት አሰፋና ጉዳፍ ፀጋዬ፣ እና ርብቃ ሀይሌ ።

ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች አምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን ለማክበርና እውቅና ለመስጠት ዝግጅቱ ተጠናቋል፤ በስፖርቱ ዘርፍ የኦሎምፒክ እና የአለም ሻምፕዮን ሜዳሊያዎች ባለቤት አትሌት መሰረት ደፋር፣ በቢዝነስ ዘርፍ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ ባለሃብቱ ጆ ማሞ፣ በስነ ጥበብ ዘርፍ አንጋፋው ድምፃዊ መሃሙድ አህመድ፣ እና ታዋቂው የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያ ሰይፉ ፋንታሁን ተሸላሚዎች ይሆናሉ።

ዝግጅቱ በጊፍት ሪል ስቴት የአቅራቢ ስፖንሰርነት የሚታገዝ ሲሆን፤ በእለቱ የዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ሴናተሮች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረጋላቸው በርካታ እንግዶች ይገኛሉ፤ ተሸላሚዎቹ ከግዛቶቹና ከተማዎቹ ተወካዮች የእውቅና ሰርተፍኬት ይበረከትላቸዋል። በተጨማሪ የሙዚቃ ዝግጅት የሚቀርብ ይሆናል። ዝግጅቱ በሜሪላንድ ስቴት ሲልቨር ስፕሪንግ በሚገኘው ሲቪክ ህንፃ ኦክቶበር 12 ምሽት በርካታ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች በሚገኙበት ይከናወናል።

(ግራንድ አፍሪካን ረን)

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

 Three-time Olympic gold medalist Gabby Thomas has arrived in the Ethiopian capital ahead of the highly anticipated Addis Ababa Grand Prix. Her arrival marks a significant milestone for the region,…

You Missed

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

Saint George respond on the pitch 

Saint George respond on the pitch