ይስማው ድሉ እና መልክናት ውዱ የ2018 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ 10 ኪሎ ሜትር አሸነፉ

ይስማው ከሁለቱ አሸናፊዎች የበለጠ አሳማኝ የነበረ ሲሆን ፤ ውድድሩን በ28 ደቂቃ ከ25 ሰከንድ አጠናቋል። ይህም በ2006 ዓ.ም በድሪባ መርጋ ከተመዘገበው የውድድሩ ሪከርድ (28፡16) በ9 ሰከንድ ብቻ ዘግይቶ አጠናቋል። ይህ ድሉ ባለፈው ቅዳሜ በተካሄደው አገር አቋራጭ ማጣሪያ ላይ ለኢትዮጵያ ቡድን ማለፍ ባለመቻሉ የተሰማውን ቁጭት ያስረሳው ሲሆን ፤ በጎዳና እና በትራክ ላይ በሚያደርጋቸው ውድድሮች ግን ባለው ስኬት ላይ ተጨማሪ ድል ሆኖለታል።

ባለፈው ዓመት 3ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ይስማው ፤ በመስከረም ወር መጨረሻ በካርዲፍ ግማሽ ማራቶን በ59 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በማሸነፍ ጥሩ አቋም ላይ ሆኖ ነበር ወደዚህ ውድድር የመጣው። በበጋው መጨረሻ ላይ ደግሞ በ3፡58.7 በሆነ ሰዓት የመንገድ ማይል በመሮጥ በተለያዩ ርቀቶች ላይ ያለውን አቅም እያሳየ የሚገኝ ወጣት አትሌት ነው። በሁለተኛ ደረጃ አዲሱ ነጋሽ (28:28) እና በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ ድንቃለም አየለ (28:29) በመግባት አጠናቀዋል።

በሴቶች ከሁለት ዓመት በፊት የውድድሩ አሸናፊ የነበረችው መልክናት ውዱ ፤ በመጨረሻዎቹ 150 ሜትሮች ላይ ፍታው ዘርዓይን በማስቀደም ወደ ቀድሞ ፎርሟ መመለሷን አረጋግጣለች። ውዱ ከሁለት ሳምንት በፊት በቦስተን ግማሽ ማራቶን ከሀገሯ ልጅ ፋንታዬ በላይነሽ በመቀጠል 2ኛ ሆና ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ ይህም በበጋው ሁለተኛ አጋማሽ በደረሰባት ጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቃ ከቆየች በኋላ ነው።

ሁለቱም አሸናፊዎች እያንዳንዳቸው 400,000 የኢትዮጵያ ብር የገንዘብ ሽልማት አግኝተዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርት ህይወታቸው በሚቀጥሉበት ጊዜ የአሸናፊነት መለያው ለእነሱ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። ድሉ ቀጣይ ውድድሩን በታህሳስ 5 በሳውዲ አረቢያ የሚያደርግ ሲሆን፣ ወዱ ደግሞ ለሚቀጥለው የቤት ውስጥ ውድድር (Indoor season) ወደ ትራክ ለመመለስ ትፈልጋለች።ዛሬ መስመሩን ከተሻገሩ የመጀመሪያዎቹ አምባሳደሮች መካከል የኖርዌይ አምባሳደር ሲሆኑ፣ ውድድሩን በ49 ደቂቃ ከ3 ሰከንድ አጠናቀዋል።

ለታላቁ የኢትዮጵያ ሩጫ ተጋባዥ እንግዶች ሆነው የቀረቡት ዳንኤል ኮመን እና ኻሊድ ኻኑቺ ከብዙሃኑ ጋር ኮርሱን ያጠናቀቁ ሲሆን፣ በ44 ደቂቃ እና በ50 ደቂቃ በመግባት ውድድሩን አጠናቀዋል።

🥇 አሸናፊ ወንዶች

  1. ይስማው ድሉ 28:25.2
  2. አዲሱ ነጋሽ 28:28.6
  3. ድንቃለሙ አየለ28:29.2

🥇ሴቶች ሰዓት

  1. መልክናት ውዱ 32:11.2
  2. ፍታው ዘራይ 32:11.5
  3. መሰለች አለማየሁ 32:19.7

Via Great Ethiopian Run

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

    via Great African Run ዋሽንግተን ዲሲ:- ዝነኛው የኬንያ የረጅም ርቀት ሯጭ ፖል ቴርጋት ኦክቶበር 10 ቀን 2026 በአሌክሳንድሪያ፣ ቨርጂኒያ በሚካሄደው ግራንድ አፍሪካን ረን የክብር እንግዳ ሆኖ እንደሚሳተፍ አዘጋጆቹ አስታወቁ። ፖል…

    Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

    Addisu Gobena wins Sydney Marathon with course-record performance Ethiopian athlete Addisu Gobena won the Sydney Marathon on Saturday August 30, setting a new course record at the World Athletics Platinum Label event.…

    You Missed

    ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

    ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

    Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

    Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

    Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

    Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

    Abubeker Nassir has joined Mechal

    Abubeker Nassir has joined Mechal

    Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

    Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

    የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

    የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።