ለኤሊት የጨዋታ አመራሮች የኢንተርናሽናል ዳኝነት ደረጃ ፈተና ተሰጠ

  • News
  • September 17, 2021
  • 0 Comments

(እግር ኳስ ፌዴሬሽን)

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ልማትና አስተዳዳር ዳይሬክቶሬት ከዳኞች ልማት ኮሚቴ ጋር በመቀናጀት በ2022 የውድድር ዘመን በኢንተርናሽናል ደረጃ እግር ኳስን መምራት የሚችሉ ዳኞችን ለመለየት ለ12 ኤሊት ወንዶችና ሴቶች የጨዋታ አመራሮች/ ዳኞች/ ትናንት መስከረም 6 ቀን 2014 ዓ.ም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት የጽሑፍ፣ የቃልና የኮምፒውተር ክህሎት ፈተና አካሄደ፡፡

ፈተናው መስከረም 5 ቀን 2014 ዓ.ም በተደረገው የኢንተርናሽናል እና የኤሊት የጨዋታ አመራሮች የአካል ብቃት ፈተና ውጤት ማለፋቸውን ለአረጋገጡ 12 ኤሊት ዳኞች የተሰጠ ሲሆን ከነዚህም አንድ ሴት ዋና ዳኛ ፣ ከወንዶች 7 ዋና እና 4 ረዳት ዳኞች ይገኙበታል፡፡


ለኤሊት ዳኞች የተዘጋጀው ፈተና ዓላማ ቀደም ሲል በኢንተርናሽናል ደረጃ የነበሩት ዋና እና ረዳት ዳኞች ቁጥር በተለያዩ ምክንያት በመቀነሱ እነሱን ለመተካት የተዘጋጀ ሲሆን በመመዘኛ ፈተናዎቹ እና በቀረበው መስፈርት መሰረት የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ኤሊት ዳኞችን ወደ ኢንተርናሽናል የጨዋታ አመራር ደረጃ ብቃት በመመዘን ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው፡፡


በኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2021 በዓለም አቀፋ እግር ኳስ ማህበር /ፊፋ/ ኮታ መሠረት በዋና ዳኝነት 7 ወንድ እና 4 ሴት፣ በረዳት ዳኝነት በተመሳሳይ 7 ወንድ እና 4 ሴት በአጠቃላይ 11 ኢንተርናሽናል ዋና እና 11 ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኞች ተመዝግበው ባጅ ከወሰዱት መካከል 4 ዳኞች በተለያዩ ምክንያቶች በመቀነሳቸው እነዚህን ለመተካት በተዘጋጀው የኤሊቶች ፈተና የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ 4 ዳኞች ( አንድ /1/ ሴት ዋና ዳኛ እንዲሁም 2 ዋና 1 ረዳት ወንዶች) ዳኞች ለ2022 በኢንተርናሽናል ዳኝነት ዝርዝር ውስጥ የሚካተቱ ይሆናል፡፡

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

Gudaf Tsegay banned for four months

Decorated two-time former World champion and Olympic medallist, Gudaf Tsegay, has been banned for four months by the Athletics Integrity Unit (AIU) under a Case Resolution Agreement, after admitting to…

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

The Ethiopia national under-17 football team will face Mozambique national under-17 football team in a play-off match that will determine qualification for the FIFA U-17 World Cup. Ethiopia defeated Tunisia…

Leave a Reply

You Missed

Gudaf Tsegay banned for four months

Gudaf Tsegay banned for four months

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia U17 to Face Mozambique in World Cup Play-Off

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

Ethiopia Learns Fate in AFCON 2027 Qualification Draw

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

CBE Crowned Women’s Premier League Champions

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

Ethiopia U17 Faces Morocco in Crucial AFCON Encounter

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች