በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዙሪያ የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት ምን ይላል?

ከአራት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብን “የታገዱ ተጫዋቾችን በማሰለፍ” በሚል በኢትዮጵያ ዋንጫ ያገኘው ድል ተሰርዞ በፎርፌ እንዲሽነፍ እና የቀጣዩ የውድድር ዘመን የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳታፊነቱ እንዲነጠቅ መወሰኑ ይታወሳል። በዚህም ክለቡ ለዓለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት /ካስ/ ይግባኝ እንደጠየቀ መግለፁ ይታወቃል።

ይግባኙ ምን ላይ ደርሷል?

ካስ በገላጋዮች የሚሰሙ ክርክሮችን ዝርዝር በየሳምንቱ ወይም እንደ አስፈላጊነቱ በድረ ገፁ ያወጣል። የሲዳማ ቡና ጉዳይ ግን እስካሁን ድረስ በዚህ ዝርዝር ውስጥ አልተካተተም።  ካስ ይግባኙ ደርሶት እንደሆነ እና ክርክሩ መቼ ሊሰማ እንደሚችል ጠይቄያለሁ። 

ካስ በምላሹ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ላይ ያቀረበውን ይግባኝ ሐምሌ ስምንት ቀን 2017 ዓ.ም መቀበሉን አረጋግጧል። 

በአሁኑ ወቅት ሁለቱ ተከራካሪዎች ጉዳያቸውን በፅሁፍ እያቀረቡ እንደሆነም ካስ ገልፅዋል። ይህ ወቅት ሁለቱ ወገኖች ክርክራቸውን፣ ማስረጃዎቻቸውን እና የህግ ምክንያቶቻቸውን በፅሁፍ ለካስ የሚያቃርቡበት ጊዜ ነው።

ሆኖም ካስ ክርክሩን የመስሚያ ቀን አልቆረጠለትም። ካስ ክርክሩን የመስሚያ ቀን እንደወሰነ በድረ ገፁ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች የ4 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ‘ሌሎችን ለመርዳት እሮጣለሁ’ በተሰኘው የ2018 ሶፊማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለምአቀፍ 10ኪ.ሜ. የበጎ አድራጎት ዘመቻው አማካኝነት ያሰባሰበውን 4 ሚሊዮን ብር በቼሻየር ኢትዮጵያ መናገሻ ቢሮ በተከናወነ ደማቅ ስነ-ስርዓት ለተመረጡ…

You Missed

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

Saint George respond on the pitch 

Saint George respond on the pitch