በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዙሪያ የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት ምን ይላል?

ከአራት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብን “የታገዱ ተጫዋቾችን በማሰለፍ” በሚል በኢትዮጵያ ዋንጫ ያገኘው ድል ተሰርዞ በፎርፌ እንዲሽነፍ እና የቀጣዩ የውድድር ዘመን የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳታፊነቱ እንዲነጠቅ መወሰኑ ይታወሳል። በዚህም ክለቡ ለዓለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት /ካስ/ ይግባኝ እንደጠየቀ መግለፁ ይታወቃል።

ይግባኙ ምን ላይ ደርሷል?

ካስ በገላጋዮች የሚሰሙ ክርክሮችን ዝርዝር በየሳምንቱ ወይም እንደ አስፈላጊነቱ በድረ ገፁ ያወጣል። የሲዳማ ቡና ጉዳይ ግን እስካሁን ድረስ በዚህ ዝርዝር ውስጥ አልተካተተም።  ካስ ይግባኙ ደርሶት እንደሆነ እና ክርክሩ መቼ ሊሰማ እንደሚችል ጠይቄያለሁ። 

ካስ በምላሹ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ላይ ያቀረበውን ይግባኝ ሐምሌ ስምንት ቀን 2017 ዓ.ም መቀበሉን አረጋግጧል። 

በአሁኑ ወቅት ሁለቱ ተከራካሪዎች ጉዳያቸውን በፅሁፍ እያቀረቡ እንደሆነም ካስ ገልፅዋል። ይህ ወቅት ሁለቱ ወገኖች ክርክራቸውን፣ ማስረጃዎቻቸውን እና የህግ ምክንያቶቻቸውን በፅሁፍ ለካስ የሚያቃርቡበት ጊዜ ነው።

ሆኖም ካስ ክርክሩን የመስሚያ ቀን አልቆረጠለትም። ካስ ክርክሩን የመስሚያ ቀን እንደወሰነ በድረ ገፁ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዛሬ የ2019 ዓ.ም. ዓለም አቀፍ 10 ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባን በይፋ አስጀምሯል። ውድድሩ እሑድ ህዳር 13 ቀን 2019 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን፣ በዚህ ዓመት በታሪኩ ከፍተኛውን 60,000…

የጀርመን ስንብት ሲቃኝ

የጀርመን ብሄራዊ ቡድን ከ2026ቱ የአለም ዋንጫ በፓራጏይ 4-3 በፍፁም ቅጣት ምት ተረቶ ተሰናብቷል::  በዚህም መሀል አሰልጣኝ ጁሊያን ናግልስማን ከባድ ትችት እየገጠመው ነው::  የቀድሞው የጀርመን እና አርሰናል ግብ ጠባቂ የንስ ሌማን…

You Missed

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Abubeker Nassir has joined Mechal

Abubeker Nassir has joined Mechal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።