አለም አትሌቲክስ እና የሴቶች የፆታ ምርመራ ጉዳይ

ባለፈው አመት በፓሪስ በተካሄደው የኦሎምፒክ ውድድር አልጄሪያዊቷ አትሌት ኢማን ካሊፍ ከፆታ ተገቢነት አንፃር በርካታ ጥያቄዎች ሲነሱባት እንደነበር የሚታወስ ነው:: 

ከዚህ በመቀጠልም በሌሎች ውድድሮች ለመሳተፍ ግዴታ ምርመራ ማድረግ እንዳለባት የሚገልፁ ደንቦች ወጥተዋል:: 

የአለም አትሌቲክስ ማህበር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ መሰረትም አትሌቶች ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚደረግ የፆታ ምርመራ ማከናወን ይጠበቅባቸዋል:: 

ይህ ምርመራ የወንዱ Y ክሮሞዞም ላይ የሚገኘውን SRY ዘረ መል ወይንም በተለምዶ ‘ፆታ የሚለይ ዘረ መል ‘ የተባለውን መርምሮ ማወቅ የሚያስችል ነው::ምርመራው ከጉንጭ የውስጠኛው ክፍል በሚወሰድ ናሙና ወይንም በደም ምርመራ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

የአለም አትሌቲክስ ፕሬዝዳንት ሰባስቲያን ኮ “ የሴቶችን ስፖርት በጥንቃቄ መያዝ እና ትክክለኛነቱን መጠበቅ ያስፈልጋል” በማለት ተናግረዋል:: “በርካታ ሴቶች እንዲወዳደሩ ስለምንፈልግ ትክክለኛ አሰራሮችን መከተል አለብን” በማለትም ገልፀዋል:: 

“ የY ክሮሞዞምን ብቻ መመልከት በራሱ አንድ ሰው ሴት ወይንም ወንድ ለመሆኑ በቂ ማረጋገጫ ነው ማለት አይደለም” በማለት በማንችስተር ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት አሉን ዊልያምስ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ ይናገራሉ:: 

እንደባለሙያው ገለፃ ጥሩ ጠቋሚ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ግን አጥጋባቢ መልስ የሚሰጥ ነው ማለት አይቻልም:: 

ከፆታ አፈጣጠር ጋር ተያይዞ ህመም ያለባቸው ሰዎች ያላቸው Y ክሮሞዞም በበቂ ሁኔታ የዳበረ አይደለም:: የተወሰኑ የተሰወሩ የዘረ መል አካላት ሊኖሩ ይችላሉ:: 

SRY ዘረ መልን ማወቅ ግን ከY ክሮሞዞም በተሻለ ጥሩ ምልክቶችን ይሰጣል:: 

ተጨማሪ የቴስቴስትሮን ንጥረ ነገር መያዝ ከሚሰጣቸው ጥቅሞች መካከል ተለቅ ያለ የጡንቻ ግዝፈት : የጠነከሩ እና የረዘሙ አጥንቶች እንደዚሁም እንደሳንባ እና ልብ ያሉ የሰውነት አካላት መጨመርም ይካታቱበታል:: እነዚህ የተለዩ ጥቅሞች ያላቸው አትሌቶች በሴቶች ስፖርት በመግባት ውድድሩን የአንድ ወገን ብቻ እንዳያደርጉት እየሰራሁ ነው በማለት የአለም አትሌቲክስ ገልፆል:: 

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች የ4 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ‘ሌሎችን ለመርዳት እሮጣለሁ’ በተሰኘው የ2018 ሶፊማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለምአቀፍ 10ኪ.ሜ. የበጎ አድራጎት ዘመቻው አማካኝነት ያሰባሰበውን 4 ሚሊዮን ብር በቼሻየር ኢትዮጵያ መናገሻ ቢሮ በተከናወነ ደማቅ ስነ-ስርዓት ለተመረጡ…

    You Missed

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

    Saint George respond on the pitch 

    Saint George respond on the pitch