አለም አትሌቲክስ እና የሴቶች የፆታ ምርመራ ጉዳይ

ባለፈው አመት በፓሪስ በተካሄደው የኦሎምፒክ ውድድር አልጄሪያዊቷ አትሌት ኢማን ካሊፍ ከፆታ ተገቢነት አንፃር በርካታ ጥያቄዎች ሲነሱባት እንደነበር የሚታወስ ነው:: 

ከዚህ በመቀጠልም በሌሎች ውድድሮች ለመሳተፍ ግዴታ ምርመራ ማድረግ እንዳለባት የሚገልፁ ደንቦች ወጥተዋል:: 

የአለም አትሌቲክስ ማህበር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ መሰረትም አትሌቶች ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚደረግ የፆታ ምርመራ ማከናወን ይጠበቅባቸዋል:: 

ይህ ምርመራ የወንዱ Y ክሮሞዞም ላይ የሚገኘውን SRY ዘረ መል ወይንም በተለምዶ ‘ፆታ የሚለይ ዘረ መል ‘ የተባለውን መርምሮ ማወቅ የሚያስችል ነው::ምርመራው ከጉንጭ የውስጠኛው ክፍል በሚወሰድ ናሙና ወይንም በደም ምርመራ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

የአለም አትሌቲክስ ፕሬዝዳንት ሰባስቲያን ኮ “ የሴቶችን ስፖርት በጥንቃቄ መያዝ እና ትክክለኛነቱን መጠበቅ ያስፈልጋል” በማለት ተናግረዋል:: “በርካታ ሴቶች እንዲወዳደሩ ስለምንፈልግ ትክክለኛ አሰራሮችን መከተል አለብን” በማለትም ገልፀዋል:: 

“ የY ክሮሞዞምን ብቻ መመልከት በራሱ አንድ ሰው ሴት ወይንም ወንድ ለመሆኑ በቂ ማረጋገጫ ነው ማለት አይደለም” በማለት በማንችስተር ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት አሉን ዊልያምስ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ ይናገራሉ:: 

እንደባለሙያው ገለፃ ጥሩ ጠቋሚ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ግን አጥጋባቢ መልስ የሚሰጥ ነው ማለት አይቻልም:: 

ከፆታ አፈጣጠር ጋር ተያይዞ ህመም ያለባቸው ሰዎች ያላቸው Y ክሮሞዞም በበቂ ሁኔታ የዳበረ አይደለም:: የተወሰኑ የተሰወሩ የዘረ መል አካላት ሊኖሩ ይችላሉ:: 

SRY ዘረ መልን ማወቅ ግን ከY ክሮሞዞም በተሻለ ጥሩ ምልክቶችን ይሰጣል:: 

ተጨማሪ የቴስቴስትሮን ንጥረ ነገር መያዝ ከሚሰጣቸው ጥቅሞች መካከል ተለቅ ያለ የጡንቻ ግዝፈት : የጠነከሩ እና የረዘሙ አጥንቶች እንደዚሁም እንደሳንባ እና ልብ ያሉ የሰውነት አካላት መጨመርም ይካታቱበታል:: እነዚህ የተለዩ ጥቅሞች ያላቸው አትሌቶች በሴቶች ስፖርት በመግባት ውድድሩን የአንድ ወገን ብቻ እንዳያደርጉት እየሰራሁ ነው በማለት የአለም አትሌቲክስ ገልፆል:: 

  • Brook Genene

    Brook is a football writer who focuses on sports injuries. He has previously written on local sports for Soccer Ethiopia and Ethiopian Business Review magazine.

    Related Posts

    የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

    ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዛሬ የ2019 ዓ.ም. ዓለም አቀፍ 10 ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባን በይፋ አስጀምሯል። ውድድሩ እሑድ ህዳር 13 ቀን 2019 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን፣ በዚህ ዓመት በታሪኩ ከፍተኛውን 60,000…

    የጀርመን ስንብት ሲቃኝ

    የጀርመን ብሄራዊ ቡድን ከ2026ቱ የአለም ዋንጫ በፓራጏይ 4-3 በፍፁም ቅጣት ምት ተረቶ ተሰናብቷል::  በዚህም መሀል አሰልጣኝ ጁሊያን ናግልስማን ከባድ ትችት እየገጠመው ነው::  የቀድሞው የጀርመን እና አርሰናል ግብ ጠባቂ የንስ ሌማን…

    You Missed

    ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

    ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

    Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

    Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

    Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

    Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

    Abubeker Nassir has joined Mechal

    Abubeker Nassir has joined Mechal

    Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

    Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

    የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

    የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።