አስተያየት፡ ነጋዴ ክለቦች እንዲኖሩን

አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ክለቦች በመንግስት ቀጥተኛ በጀት የሚተዳደሩ ናቸው:: ነገር ግን መንግስት ለክለቦች ቀጥተኛ በጀት መስጠት ቀስ በቀስ ማቆም እንዳለበት አምናለሁ። ምክንያቱም በምቹ ሁኔታዎች ውስጥ ክለቦች የራሳቸውን ገቢ ማግኘት ይችላሉ። ይህም ስፖርቱን ለትርፍ መጠቀም የሚፈልጉ ባለሀብቶችን ወደ እግር ኳሱ ያመጣቸዋል። ነገር ግን በኢትዮጵያ የስፖርት ክለቦች የንግድ ተቋም መሆን የሚችሉ አይመስልም።

ህጉ ምን ይላል?

በተለምዶ መመሪያ አንድ የሚባለው በወቅቱ በነበረው ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማህበራት ስለሚቋቋሙበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣው መመሪያ ቁጥር 1/2003 ስለ ስፖርት ክለቦች አመሰራረት አንድ አንቀፅ ይዞ ነበር። የመመሪያው አንቀፅ 14 የስፖርት ክለቦች ስፖርቱን ለንግድ (ለትርፋማነት) በሚጠቀሙ ባለሀብቶች ሊመሰረቱ እንደሚችሉ ይደነግጋል። ከዚያ ቀጥሎ በተሻሻሉት መመሪያ 75/2013 እና 622/2014 ግን ይህ አንቀፅ ሙሉ ለሙሉ እንዲቀር ተደርጓል።

ታዲያ መመሪያው ፈቅዶ ከነበረ ነጋዴ ክለቦች ለምን አልተቋቋሙም?

ነጋዴ የሆናችሁ እንደምታውቁት የንግድ ፈቃድ ስታወጡ የንግድ ስራ መስክ /field of business/ እና የተሰማራችሀብት የንግድ ስራ /type of activity/ በንግድ ፈቃዳችሁ እና በምዝገባ የምስክር ወረቀታችሁ ላይ ይኖራል። የንግድ ስራ መስኩ እና የንግድ ስራው ደግሞ ራሳቸውን የቻለ “ኮድ” ይኖራቸዋል። የንግድ ፈቃድ እና ምዝገባ የሚሰጠው ደግሞ በንግድ ምዝገባና የፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008 መሰረት ሆኖ ድርጅቱ የሚሰማራበት የንግድ ዘርፍ ኮድ የሚሰጠው ደግሞ የኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያ ቁጥር 556/2013 መሰረት ነው። ይህ መመሪያ የስፖርት ክለብነትን እንደ የንግድ ዘርፍ አያውቀውም። ከዚህ መመሪያ በፊት በ2003 እና በ2005 የወጡት የኢትዮጵያ ንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያዎችም የስፖርት/እግር ኳስ ክለብነትን እንደ የንግድ ዘርፍ አይመለከቱትም ነበር። ስለዚህ የቀድሞው የስፖርት ማህበራት ስለሚቋሙበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣው መመሪያ ነጋዴ ክለቦች እንዲኖሩ ቢፈቅድም የኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያዎች ግን የስፖርት ክለብ ወይም የእግር ኳስ ክለብ የሚባልን የንግድ ዘርፍ አያውቁም።

አዲሱ የባህልና ስፖርት መመሪያ እና የክለቦች እጣ ፈንታ

ሀገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ስለሚቋቋሙበት ሁኔታ ለመወሰን ተሻሽሎ የወጣው መመሪያ ቁጥር 907/2014 በመመሪያ ቁጥር አንድ የነበረውን የስፖርት ክለቦች ስለሚቋቋሙበት ሁኔታ የሚወስነውን አንቀፅ ሙሉ ለሙሉ አስቀርቶታል። በዚህም የክለቦችን ጉዳይ ለፌዴሬሽኖች የሰጠ ይመስላል።

“የስፖርት ክለብንም “በአባላት እና በስፖርተኞች ስብስብ ስፖርትን ለማራመድ ከስፖርት ማህበር ፈቃድ ተሰጥቶት የተቋቋመ ነው” የሚል ብያኔ ይሰጠዋል። ፌዴሬሽኖች በሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ፈቃድ የሚሰጣቸው የስፖርት ማህበራት ናቸው። በእርግጥ በቀድሞው መመሪያም ክለቦች ፈቃድ የሚያገኙት ከፌዴሬሽኖች ነበር። ሆኖም ክለቦቹ ቢያንስ ህጋዊ እውቅና ለማግኘት ሊያሟሏቸው የሚገቧቸው መመዘኛዎች ግን በአዲሱ መመሪያ ቀርተዎል። አሁን ይህን መወሰን በመመሪያ ቁጥር 907/2014 አንቀፅ 8 (3) መሰረት የፌዴሬሽኖች ስልጣን ነው። ይህ ግን በመመሪያው አንቀፅ 59 የተከለከሉ ተግባራትን አይጨምርም።

ይህ ፈቃድ ሙሉ ለሙሉ ወደ ፌዴሬሽኖች መሄዱ የእግር ኳስ ክለቦችን የበለጠ ያግዛል የሚል እምነት አለኝ:: ምክንያቱም ንግድ ፈቃድ ለማውጣት የብቃት ማረጋግጫ ለማግኘት የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑን የክለብ ላይሰንሲንግ መመሪያዎች ማክበር በቂ ሊሆን ይችላል:: ስለዚህ የእግር ኳስ ክለብነት በኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያ እንደ አንድ የንግድ ዘርፍ እንዲካተት ማድርግ ክለቦች እና ፌዴሬሽኑ በጋራ መስራት ይችላሉ:: ክለቦቻችሁ ወደ ንግድ ተቋምነት እንዲቀየሩ የምትፈልጉ አቅም ያላችሁ ደጋፊዎችም ከክለቦቹ ጋር ከመከራከር መጀመሪያ ከፌዴሬሽኑ ጋር በመሆን የሚመለከተው ሚንስቴር መ/ቤት ላይ ጫና በማሳደር የኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያ እንዲሻሻል ብታደርጉ ይሻላል:: ይህ ለምን የንግድ ተቋም እንደማይሆኑ ሲጠየቁ “ህጉ አይፈቅድም” በሚል መልስ የሚደበቁ ክለቦችንም ሰበባቸውን ያስቀራል:: ያው ከልብ ካዘኑ…

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን በ2ሰአት 15 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በመጨረስ የራሷን የሴቶች ብቻ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡  ትዕግስት የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊዋን ሄለን ኦቢሪ እና የ2021 የለንደን ማራቶችን…

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

 Three-time Olympic gold medalist Gabby Thomas has arrived in the Ethiopian capital ahead of the highly anticipated Addis Ababa Grand Prix. Her arrival marks a significant milestone for the region,…

You Missed

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

ትዕግስት አሰፋ የራሷን የማራቶን ክብረ ወሰን አሻሽላለች 

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Olympic Champion Gabby Thomas Touches Down in Addis Ababa for Historic Grand Prix

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

Doha Diamond League Postponed to June; Venue Switched to Khalifa International Stadium

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

የአለም አትሌቲክስ ከ2030 ጀምሮ ራሱን የቻለ የአለም ማራቶን ሻምፒዮና ሊያስተዋውቅ ነው

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

World Athletics to introduce standalone World Marathon Championships from 2030 

Saint George respond on the pitch 

Saint George respond on the pitch