አስተያየት፡ ነጋዴ ክለቦች እንዲኖሩን

አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ክለቦች በመንግስት ቀጥተኛ በጀት የሚተዳደሩ ናቸው:: ነገር ግን መንግስት ለክለቦች ቀጥተኛ በጀት መስጠት ቀስ በቀስ ማቆም እንዳለበት አምናለሁ። ምክንያቱም በምቹ ሁኔታዎች ውስጥ ክለቦች የራሳቸውን ገቢ ማግኘት ይችላሉ። ይህም ስፖርቱን ለትርፍ መጠቀም የሚፈልጉ ባለሀብቶችን ወደ እግር ኳሱ ያመጣቸዋል። ነገር ግን በኢትዮጵያ የስፖርት ክለቦች የንግድ ተቋም መሆን የሚችሉ አይመስልም።

ህጉ ምን ይላል?

በተለምዶ መመሪያ አንድ የሚባለው በወቅቱ በነበረው ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማህበራት ስለሚቋቋሙበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣው መመሪያ ቁጥር 1/2003 ስለ ስፖርት ክለቦች አመሰራረት አንድ አንቀፅ ይዞ ነበር። የመመሪያው አንቀፅ 14 የስፖርት ክለቦች ስፖርቱን ለንግድ (ለትርፋማነት) በሚጠቀሙ ባለሀብቶች ሊመሰረቱ እንደሚችሉ ይደነግጋል። ከዚያ ቀጥሎ በተሻሻሉት መመሪያ 75/2013 እና 622/2014 ግን ይህ አንቀፅ ሙሉ ለሙሉ እንዲቀር ተደርጓል።

ታዲያ መመሪያው ፈቅዶ ከነበረ ነጋዴ ክለቦች ለምን አልተቋቋሙም?

ነጋዴ የሆናችሁ እንደምታውቁት የንግድ ፈቃድ ስታወጡ የንግድ ስራ መስክ /field of business/ እና የተሰማራችሀብት የንግድ ስራ /type of activity/ በንግድ ፈቃዳችሁ እና በምዝገባ የምስክር ወረቀታችሁ ላይ ይኖራል። የንግድ ስራ መስኩ እና የንግድ ስራው ደግሞ ራሳቸውን የቻለ “ኮድ” ይኖራቸዋል። የንግድ ፈቃድ እና ምዝገባ የሚሰጠው ደግሞ በንግድ ምዝገባና የፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008 መሰረት ሆኖ ድርጅቱ የሚሰማራበት የንግድ ዘርፍ ኮድ የሚሰጠው ደግሞ የኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያ ቁጥር 556/2013 መሰረት ነው። ይህ መመሪያ የስፖርት ክለብነትን እንደ የንግድ ዘርፍ አያውቀውም። ከዚህ መመሪያ በፊት በ2003 እና በ2005 የወጡት የኢትዮጵያ ንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያዎችም የስፖርት/እግር ኳስ ክለብነትን እንደ የንግድ ዘርፍ አይመለከቱትም ነበር። ስለዚህ የቀድሞው የስፖርት ማህበራት ስለሚቋሙበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣው መመሪያ ነጋዴ ክለቦች እንዲኖሩ ቢፈቅድም የኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያዎች ግን የስፖርት ክለብ ወይም የእግር ኳስ ክለብ የሚባልን የንግድ ዘርፍ አያውቁም።

አዲሱ የባህልና ስፖርት መመሪያ እና የክለቦች እጣ ፈንታ

ሀገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ስለሚቋቋሙበት ሁኔታ ለመወሰን ተሻሽሎ የወጣው መመሪያ ቁጥር 907/2014 በመመሪያ ቁጥር አንድ የነበረውን የስፖርት ክለቦች ስለሚቋቋሙበት ሁኔታ የሚወስነውን አንቀፅ ሙሉ ለሙሉ አስቀርቶታል። በዚህም የክለቦችን ጉዳይ ለፌዴሬሽኖች የሰጠ ይመስላል።

“የስፖርት ክለብንም “በአባላት እና በስፖርተኞች ስብስብ ስፖርትን ለማራመድ ከስፖርት ማህበር ፈቃድ ተሰጥቶት የተቋቋመ ነው” የሚል ብያኔ ይሰጠዋል። ፌዴሬሽኖች በሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ፈቃድ የሚሰጣቸው የስፖርት ማህበራት ናቸው። በእርግጥ በቀድሞው መመሪያም ክለቦች ፈቃድ የሚያገኙት ከፌዴሬሽኖች ነበር። ሆኖም ክለቦቹ ቢያንስ ህጋዊ እውቅና ለማግኘት ሊያሟሏቸው የሚገቧቸው መመዘኛዎች ግን በአዲሱ መመሪያ ቀርተዎል። አሁን ይህን መወሰን በመመሪያ ቁጥር 907/2014 አንቀፅ 8 (3) መሰረት የፌዴሬሽኖች ስልጣን ነው። ይህ ግን በመመሪያው አንቀፅ 59 የተከለከሉ ተግባራትን አይጨምርም።

ይህ ፈቃድ ሙሉ ለሙሉ ወደ ፌዴሬሽኖች መሄዱ የእግር ኳስ ክለቦችን የበለጠ ያግዛል የሚል እምነት አለኝ:: ምክንያቱም ንግድ ፈቃድ ለማውጣት የብቃት ማረጋግጫ ለማግኘት የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑን የክለብ ላይሰንሲንግ መመሪያዎች ማክበር በቂ ሊሆን ይችላል:: ስለዚህ የእግር ኳስ ክለብነት በኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያ እንደ አንድ የንግድ ዘርፍ እንዲካተት ማድርግ ክለቦች እና ፌዴሬሽኑ በጋራ መስራት ይችላሉ:: ክለቦቻችሁ ወደ ንግድ ተቋምነት እንዲቀየሩ የምትፈልጉ አቅም ያላችሁ ደጋፊዎችም ከክለቦቹ ጋር ከመከራከር መጀመሪያ ከፌዴሬሽኑ ጋር በመሆን የሚመለከተው ሚንስቴር መ/ቤት ላይ ጫና በማሳደር የኢትዮጵያ የንግድ ስራ ፈቃድ መስጫ መደብ መመሪያ እንዲሻሻል ብታደርጉ ይሻላል:: ይህ ለምን የንግድ ተቋም እንደማይሆኑ ሲጠየቁ “ህጉ አይፈቅድም” በሚል መልስ የሚደበቁ ክለቦችንም ሰበባቸውን ያስቀራል:: ያው ከልብ ካዘኑ…

Girmachew Kebede

Founder of Tilafok.com, Girmachew Kebede is a sports journalist with more than a decade of newsroom and on-air experience. He served as Deputy Editor-in-Chief at Ethio-Sport newspaper, was host and News Editor for the Bisrat Sport radio show, and worked as a football analyst with Kuas Meda. He co-created the Rigore sports show. He was also sports and political stringer for Voice of America’s Horn of Africa Service. His articles were selected among the Top 10 in Africa by the AIPS Sport Media Awards in 2018 and 2022.

Related Posts

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

via Great African Run ዋሽንግተን ዲሲ:- ዝነኛው የኬንያ የረጅም ርቀት ሯጭ ፖል ቴርጋት ኦክቶበር 10 ቀን 2026 በአሌክሳንድሪያ፣ ቨርጂኒያ በሚካሄደው ግራንድ አፍሪካን ረን የክብር እንግዳ ሆኖ እንደሚሳተፍ አዘጋጆቹ አስታወቁ። ፖል…

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Addisu Gobena wins Sydney Marathon with course-record performance Ethiopian athlete Addisu Gobena won the Sydney Marathon on Saturday August 30, setting a new course record at the World Athletics Platinum Label event.…

You Missed

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

ፖል ቴርጋት በ2026 ግራንድ አፍሪካን ረን ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ይሳተፋል

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Ethiopian Addisu Gobena wins Sydney Marathon

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Isayas Jira has emerged as the sole candidate for the EFF Presidential election 

Abubeker Nassir has joined Mechal

Abubeker Nassir has joined Mechal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

Bahir Dar stadium to host AFCON Qualifier between Ethiopia and Senegal

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።

የ2019 ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ዛሬ በይፋ ተጀመረ።