የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በክረምቱ ዝውውር ከ3 ቢሊዮን ፓውንድ በላይ አውጥተዋል::
በትላንትናው እለት በተጠናቀቀው የክረምት የዝውውር መስኮት የእንግሊዝ ክለቦች በከፍተኛ ልዩነት ከሌሎች ሊጎች በላይ ለዝውውር ገንዘብ አውጥተዋል::
ከዚህ በፊት በ2022-23 የውድድር ዘመን ተመዝግቦ ከነበረው የ2.7 ቢሊዮን ፓውንድ ወጪ የዘንድሮው ልቆ ተገኝቷል:: ይህም ማለት 20ዎቹ ክለቦች ከዚህ በፊት ከነበረው ከፍተኛ ወጪ 650 ሚሊዮን ፓውንድ የበለጠ አውጥተዋል::
የወጪ እና ገቢ ልዩነት ሲሰላ 1.2 ቢሊዮን ፓውንድ ሲሆን ይህም ከፍተኛው መጠን ሆኖ ተመዝግቧል::
እንደሮይተርስ ዘገባ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወጪ አምስቱ ታላላቅ ሊጎች የሚባሉት ስፔን ጣሊያን ጀርመን እና ፈረንሳይ ካወጡት አንፃር የ51% ድርሻ ይዟል::
ምንም እንኳን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ትርፍ ላይ የተመሰረተ ጥብቅ የፋይናንስ ህግ ቢኖረውም የክለቦቹ ከፍተኛ ወጪ ማውጣት መቻል የቴሌቭዥን ገቢያቸውን ከፍተኛነት የሚያሳይ ነው ተብሏል::





